አርእስተ ዜና
የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን አሳልፏል
Feb 1, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ 2 ሺህ 100 ተሳታፊዎች በታደሙበት በደማቅ የመክፈቻ ስነ ስርዓት በትላንትናው ዕለት በይፋ ተጀምሯል። በጉባኤው 1 ሺህ 700 የድምፅ ተሳታፊዎች እንዲሁም የ15 ሀገራት ፓርቲዎች አመራርና ተወካዮችን ጨምሮ 400 የሀገር ውስጥና የውጭ እንግዶች በተጋባዥነት መገኘታቸውም የሚታወቅ ነው። የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ጉባኤውን አስመልክቶ ለኢዜአ በሰጡት መግለጫ ጉባኤው ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ተወካዮችን ባሳተፈና በዴሞክራሲያዊነት እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለትም ጉባኤው መድረኩን የሚመሩ የፕሬዚዲየም አባላትን በመሰየም በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ በስፋት መወያየቱንና አጀንዳዎችን መርምሮ ማጽደቁንም ተናግረዋል። በዚህም የጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት እና የስብሰባ ስነ-ስርዓት ደንብ ላይ በስፋት በመወያየት በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ብለዋል። በመቀጠልም የማዕከላዊ ኮሚቴ እንዲሁም የኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚቴ ሪፖርቶች ለጉባኤው ቀርበው ሰፊ ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ መጽደቃቸውንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ ጉባኤው በፓርቲው የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ነው ያሉት። ከአንደኛ ጉባኤ ማግስት በፓርቲው በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ፈተናዎች እና ፈተናዎችን ለማለፍ የተሔደበትን ርቀት በስፋት መገምገሙንም አንስተዋል። በዚህም የብልፅግና እሳቤ እስከ ታችኛው ህብረተሰብ ክፍል መድረሱ እና እሳቤው ባህል እየሆነ መምጣቱ የተረጋገጠበት ጉባኤ መሆኑን ገልጸዋል። ጉባኤው በነገው ዕለትም ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን የፓርቲ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ጨምሮ የአመራር ምርጫ ይደረጋል ብለዋል። ለዚህም በዛሬው ዕለት አስመራጭ ኮሚቴ በመሰየም የዕለቱ ስብሰባ አሳታፊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ተናግረዋል። ጉባኤው ለመጪዎቹ ዓመታት የሚያገለግሉ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሆነም ጠቁመዋል።
አየር ኃይል አሁን ለገነባው ከፍተኛ ወታደራዊ የዝግጁነት አቅም የሙያተኛው ድርሻ የጎላ ነው - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
Feb 1, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦አየር ኃይል አሁን ለገነባው ከፍተኛ ወታደራዊ የዝግጁነት አቅም የሙያተኛው ድርሻ የጎላ መሆኑን የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ። የኢፌዴሪ አየር ኃይል ሎጀስቲክስ የእውቅና እና የምስጋና መርሃ-ግብር በአየር ኃይል መኮንኖች ክበብ አካሂዷል። ዋና አዛዡ በመርሃ-ግብሩ በመገኘት ለተቋሙ የግዳጅ አፈፃፀም ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ክፍሎች የእውቅና እና የምስጋና ሰርተፍኬት ሰጥተዋል። ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የአየር ኃይል ሎጀስቲክስ የተቋሙን የማድረግ አቅም ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገሩ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን ጠቅሰው አየር ኃይሉ ለገነባው አሁናዊ ከፍተኛ የዝግጁነት አቅም የክፍሉ ሙያተኞች ድርሻ ከፍተኛ እንደነበረ ተናግረዋል ። የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር ሎጀስቲክስ ብርጋዲየር ጄኔራል ነገራ ሌሊሳ በበኩላቸው ተቋሙ አዳዲስ የአቪዬሽን ትጥቆችን ከመታጠቅ ባለፈ ያሉትን ጠግኖ ወደ ግዳጅ በማሰማራት ረገድ ክፍሉ ያከናወነው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይነትም በሁሉም መስክ የጀመርናቸውን ስራዎች በላቀ የስራ ተነሳሽነት አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተሰጣቸውን ግዳጅ እና ተልዕኮ በብቃት ከመፈፀም ባለፈ ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን ለሰሩ ክፍሎች የእውቅና እና የምስጋና ሰርተፊኬት እንደተሰጣቸው ከመከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በክልሉ ልማትን የሚያጠናክሩ መረጃዎች ተደራሽ በማድረግ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚያጎለብቱ ተግባራት ይቀጥላሉ
Feb 1, 2025 51
ቦንጋ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የወል በሆነ መልኩ ልማትና ዕድገትን የሚያጠናክሩ መረጃዎች ተደራሽ በማድረግ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚያጎለብቱ ተግባራት እንደሚቀጥሉ የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ገለጸ። የቢሮው የበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የተግባር አፈጻጸም ላይ የመከረ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሄዷል። በዚህ ወቅት የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ፣ ቢሮው የመረጃ ተደራሽነትን ለማስፋት የመገናኛ ብዙሃን እና የኮሙኒኬሽን መዋቅሩን በማስተባበር በርካታ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል። ለአብነት ክልሉ ያሉ የልማት አቅሞች በማስተዋወቅ በኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝምና በሌሎች ሀብቶች እንዲመጡና ማህበረሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረጉን ጠቅሰዋል። እንደአገር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመቻቹ የተለያዩ ኢንሼቲቮችን ለህዝብ ለማስተዋወቅና ሀሳቡን ለማስረፅ በተከናወነው ስራ ተስፋ ሰጪ ለውጥ መምጣቱንም ጠቁመዋል። በተለይም የወል በሆነ መልኩ ዕድገትንና ልማትን የሚያጠናክሩ መረጃዎች ተደራሽ በማድረግ ረገድ ከመገናኛ ብዙሃን ጋር በመተባበር በተደረገው ጥረት የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚያጎልበቱ ተግባራት እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። በቀጣይም በዋና ዋና የልማት አጀንዳዎች፣ ሰላምን በሚገነቡና የሕዝቦች ትስስርን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ በተቀናጀ መንገድ እንደሚሰራመ አቶ የሺዋስ አብራርተዋል። በመድረኩ የተሳተፉ የመገናኛ ብዙሃንና የኮሙዩኒኬሽን አመራር አባላት በሰጡት አስተያየት፤ከለዉጡ ወዲህ መንግስት ያመቻቸውን የመገናኛ ብዙሃን ነፃነት በመጠቀም በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። በቀጣይም የአገሪቱ የልማትና ብልፅግና ጉዛ የተሳካ እንዲሆን ህብረተሰቡን በማንቃትና እውነታውን በማሳወቁ ረገድ የሚጠበቅባቸውን አንደሚወጡ ገልጸዋል። ለአንድ ቀን በተካሄደው የምክክር መድረኩ የተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ተወካዮች፣ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የኮሙዩኒኬሽን ሥራ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የሚታይ
የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን አሳልፏል
Feb 1, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ 2 ሺህ 100 ተሳታፊዎች በታደሙበት በደማቅ የመክፈቻ ስነ ስርዓት በትላንትናው ዕለት በይፋ ተጀምሯል። በጉባኤው 1 ሺህ 700 የድምፅ ተሳታፊዎች እንዲሁም የ15 ሀገራት ፓርቲዎች አመራርና ተወካዮችን ጨምሮ 400 የሀገር ውስጥና የውጭ እንግዶች በተጋባዥነት መገኘታቸውም የሚታወቅ ነው። የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ጉባኤውን አስመልክቶ ለኢዜአ በሰጡት መግለጫ ጉባኤው ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ተወካዮችን ባሳተፈና በዴሞክራሲያዊነት እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለትም ጉባኤው መድረኩን የሚመሩ የፕሬዚዲየም አባላትን በመሰየም በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ በስፋት መወያየቱንና አጀንዳዎችን መርምሮ ማጽደቁንም ተናግረዋል። በዚህም የጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት እና የስብሰባ ስነ-ስርዓት ደንብ ላይ በስፋት በመወያየት በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ብለዋል። በመቀጠልም የማዕከላዊ ኮሚቴ እንዲሁም የኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚቴ ሪፖርቶች ለጉባኤው ቀርበው ሰፊ ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ መጽደቃቸውንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ ጉባኤው በፓርቲው የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ነው ያሉት። ከአንደኛ ጉባኤ ማግስት በፓርቲው በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ፈተናዎች እና ፈተናዎችን ለማለፍ የተሔደበትን ርቀት በስፋት መገምገሙንም አንስተዋል። በዚህም የብልፅግና እሳቤ እስከ ታችኛው ህብረተሰብ ክፍል መድረሱ እና እሳቤው ባህል እየሆነ መምጣቱ የተረጋገጠበት ጉባኤ መሆኑን ገልጸዋል። ጉባኤው በነገው ዕለትም ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን የፓርቲ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ጨምሮ የአመራር ምርጫ ይደረጋል ብለዋል። ለዚህም በዛሬው ዕለት አስመራጭ ኮሚቴ በመሰየም የዕለቱ ስብሰባ አሳታፊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ተናግረዋል። ጉባኤው ለመጪዎቹ ዓመታት የሚያገለግሉ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሆነም ጠቁመዋል።
አየር ኃይል አሁን ለገነባው ከፍተኛ ወታደራዊ የዝግጁነት አቅም የሙያተኛው ድርሻ የጎላ ነው - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
Feb 1, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦አየር ኃይል አሁን ለገነባው ከፍተኛ ወታደራዊ የዝግጁነት አቅም የሙያተኛው ድርሻ የጎላ መሆኑን የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ። የኢፌዴሪ አየር ኃይል ሎጀስቲክስ የእውቅና እና የምስጋና መርሃ-ግብር በአየር ኃይል መኮንኖች ክበብ አካሂዷል። ዋና አዛዡ በመርሃ-ግብሩ በመገኘት ለተቋሙ የግዳጅ አፈፃፀም ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ክፍሎች የእውቅና እና የምስጋና ሰርተፍኬት ሰጥተዋል። ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የአየር ኃይል ሎጀስቲክስ የተቋሙን የማድረግ አቅም ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገሩ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን ጠቅሰው አየር ኃይሉ ለገነባው አሁናዊ ከፍተኛ የዝግጁነት አቅም የክፍሉ ሙያተኞች ድርሻ ከፍተኛ እንደነበረ ተናግረዋል ። የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር ሎጀስቲክስ ብርጋዲየር ጄኔራል ነገራ ሌሊሳ በበኩላቸው ተቋሙ አዳዲስ የአቪዬሽን ትጥቆችን ከመታጠቅ ባለፈ ያሉትን ጠግኖ ወደ ግዳጅ በማሰማራት ረገድ ክፍሉ ያከናወነው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይነትም በሁሉም መስክ የጀመርናቸውን ስራዎች በላቀ የስራ ተነሳሽነት አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተሰጣቸውን ግዳጅ እና ተልዕኮ በብቃት ከመፈፀም ባለፈ ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን ለሰሩ ክፍሎች የእውቅና እና የምስጋና ሰርተፊኬት እንደተሰጣቸው ከመከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያስመዘገበች ያለው ውጤት ለአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚያደርጋት ነው- የቱሪዝም ሚኒስቴር
Feb 1, 2025 61
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያስመዘገበች ያለው ውጤት ለአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚያደርጋት መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። የሀገሪቱን እድገት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንዲያስችሉ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ካሉ ዘርፎች መካከል ቱሪዝም አንዱ ነው። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ከለውጡ ወዲህ መንግስት ለቱሪዝም ልማት በተሰጠው ተኩረት በርካታ የቱሪዝም መሰረተ ልማቶች ተገንብተዋል። በአዲስ አበባ የተጀመረው ገበታ ለሸገር ፕሮጀክትን ጨምሮ የገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶችን ለአብነት አንስተዋል። በተጨማሪም ነባር የቱሪስት መዳረሻዎችን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በፍጥነት በማደስ ለጎብኚዎች ክፍት የማድረግ ስራም በትኩረት መከናወኑን አስታውቀዋል። በቱሪዝም ልማት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት ኢትዮጵያን ለአፍሪካ ሀገራትም ጭምር ምሳሌ የሚያደርጋት መሆኑን አመልክተዋል። ለዚህም የኢጋድ አባል ሀገራት የሚመሩበት የዘላቂ ቱሪዝም ማስተር ፕላን አዲሰ አበባ ላይ ይፋ መደረጉ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ከዚህም በተጨማሪ ዘርፉ የታለመለትን አገራዊ ስኬት የበለጠ እንዲያስመዘግብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሪፎርምና መሰል የማሻሻያ ስራዎችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው አስታውቀዋል፡፡ ላለፉት 15 ዓመታት ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የቱሪዝም ፖሊሲን የመከለስ ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቅርቡም አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ ይፋ የሚደረግ መሆኑን ጠቁመዋል።
ፖለቲካ
የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን አሳልፏል
Feb 1, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ 2 ሺህ 100 ተሳታፊዎች በታደሙበት በደማቅ የመክፈቻ ስነ ስርዓት በትላንትናው ዕለት በይፋ ተጀምሯል። በጉባኤው 1 ሺህ 700 የድምፅ ተሳታፊዎች እንዲሁም የ15 ሀገራት ፓርቲዎች አመራርና ተወካዮችን ጨምሮ 400 የሀገር ውስጥና የውጭ እንግዶች በተጋባዥነት መገኘታቸውም የሚታወቅ ነው። የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ጉባኤውን አስመልክቶ ለኢዜአ በሰጡት መግለጫ ጉባኤው ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ተወካዮችን ባሳተፈና በዴሞክራሲያዊነት እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለትም ጉባኤው መድረኩን የሚመሩ የፕሬዚዲየም አባላትን በመሰየም በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ በስፋት መወያየቱንና አጀንዳዎችን መርምሮ ማጽደቁንም ተናግረዋል። በዚህም የጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት እና የስብሰባ ስነ-ስርዓት ደንብ ላይ በስፋት በመወያየት በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ብለዋል። በመቀጠልም የማዕከላዊ ኮሚቴ እንዲሁም የኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚቴ ሪፖርቶች ለጉባኤው ቀርበው ሰፊ ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ መጽደቃቸውንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ ጉባኤው በፓርቲው የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ነው ያሉት። ከአንደኛ ጉባኤ ማግስት በፓርቲው በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ፈተናዎች እና ፈተናዎችን ለማለፍ የተሔደበትን ርቀት በስፋት መገምገሙንም አንስተዋል። በዚህም የብልፅግና እሳቤ እስከ ታችኛው ህብረተሰብ ክፍል መድረሱ እና እሳቤው ባህል እየሆነ መምጣቱ የተረጋገጠበት ጉባኤ መሆኑን ገልጸዋል። ጉባኤው በነገው ዕለትም ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን የፓርቲ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ጨምሮ የአመራር ምርጫ ይደረጋል ብለዋል። ለዚህም በዛሬው ዕለት አስመራጭ ኮሚቴ በመሰየም የዕለቱ ስብሰባ አሳታፊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ተናግረዋል። ጉባኤው ለመጪዎቹ ዓመታት የሚያገለግሉ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሆነም ጠቁመዋል።
የተርኪዬ ኤኬ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዛፈር ሲራካያ ምን አሉ
Feb 1, 2025 45
  ኢትዮጵያ ከዓለማችን ጥንታዊ ስልጣኔዎች አንዷ ናት። ኢትዮጵያ በአፍሪካ የታሪክ ገጾች ውስጥ ጉልህ ታሪክ የጻፈች እንዲሁም በባህል፣ በታሪክ፣ በብዝሃነት፣ በእምነት፣ በቋንቋና ቅርስ የበለጸገችና በፈተናዎች ሳትበገር ዘመናትን የተሻገረች ሀገር ናት። ተርኪዬና ኢትዮጵያ የነጻነትና ሉዓላዊነት የአይበገሬነት መንፈስ የሚጋሩ ሀገራት ናቸው። ኢትዮጵያ እና ተርኪዬ በታሪክ ጥብቅ ቁርኝነት አላቸው። ተርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር አጠናክራ ትቀጥላለች። ኢትዮጵያ እና ተርኪዬ በዘመናት መካከል የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸው እና ትብብራቸው እያደገ መምጣቱንና በርካታ ስኬቶች እያስመዘገበ ይገኛል። ተርኪዬ ለቀጣናው ሰላምና ልማት መረጋገጥ አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ያነሷቸው ሃሳቦች ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ቀጣናውና የአፍሪካን ብልፅግናን ዕውን ማድረግ የሚያስችሉ ናቸው።
የካዛኪስታን የታችኛው ምክር ቤት እና የገዢው አማናት ፓርቲ አባል ሳማት ኑርታዛ ምን አሉ
Feb 1, 2025 57
  ኢትዮጵያ ለካዛኪስታን ታማኝ እና እውነተኛ አጋር ናት። ከኢትዮጵያ ጋር የሁለትዮሽ፣ የባለብዝሃ ወገን እና ሁሉን አቀፍ ትብብሯን ለማጠናከር ትሻለች። ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ለቀጣናው እና ዓለም አቀፍ ደህንነት ቁልፍ አበርክቶ አድርጋለች። የብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፍቷል። ብልጽግና ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ረገድ ስኬታማ ተግባር አከናውኗል። አማናት ፓርቲ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ያለውን ግንኙነት እና ካዛኪስታን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር ለማጎልበት ይሰራል። አማናት ለዓለም ሰላም እና ብልጽግና ከብልጽግና ፓርቲ ጋር በትብብር መስራት ይሻል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር ሰጪነት ብልጽግና ፓርቲ የለውጥ እና የሽግግር ተምሳሌት መሆን ችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፖለቲካ ቁርጠኝነት እና ባለ ራዕይ መሪነት፤ ውጤታማ አስተዳደር ሀገርን ከቀውስ በማውጣት ለዘላቂ ልማት መሰረት መጣል እንደሚቻል በግልጽ ያመላከተ ነው።
የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ለብልጽግና ፓርቲ 2ኛ ጉባዔ የመልካም ምኞት መልዕክት ላከ
Feb 1, 2025 70
አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2017(ኢዜአ)፦የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ለብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ የድጋፍና የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፏል፡፡ ኢትዮጵያ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት እያስመዘገበችው ላለው ሁለንተናዊ እድገት የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ (CPC) ያለውን አድናቆት ገልጿል። ቻይና የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጦ ብልጽግና ፓርቲ ኢትዮጵያ ተስማሚ የሆነ የእድገትና የዘመናዊነት መንገድ እንድትከተል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ጠቅሷል፡፡ ለአብነትም በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ የዜጎችን ኑሮ በማሻሻል፣ በአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ ዘላቂ የአካባቢ ጥበቃን በማሳደግ፣ የሀገራዊ ምክክር ቅድመ-ዝግጅት በማገባደድና ማህበራዊ አንድነትን በማጎልበት ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶች ጉልህ መሀኖቸውን ጠቅሷል። እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያን “የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት” እንድትሆን እያስቻሉ ነው ሲልም እውቅና ሰጥቷል፡፡ በቀጣይ ዓመታት ብልጽግና ፓርቲ ሀገሪቱን ወደ “አዲስና የላቀ ስኬት” መምራቱን እንደሚቀጥል ያለውን እምነት ገልጿል፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ላለው ጥልቅ ትብብር አጽንኦት በመስጠትም የሁለቱ ፓርቲዎች መሪዎች ከዚህ ቀደም የደረሱባቸውን ስምምነቶች ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝቧል፡፡ በቀጣይ የቻይናን እና የኢትዮጵያን ትብብር በሁሉም ዘርፎች በማስፋት በማንኛውም ሁኔታ የማይናወጥ ስትራቴጂያዊ አጋርነት ሆኖ የበለጠ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርቧል። ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ የኢትዮጵያን ቀጣይ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ፍኖተ ካርታ የሚቀርፅበት ወሳኝ ሁነት እንደሆነ እና ለሀገራዊ ልማት ወሳኝ የሆኑ ቀጣይ ግቦችን እንደሚቀመጡ እምነት እንዳለው በመጥቀስ ለጉባኤው ስኬት መልካሙን ሁሉ ተመኝቷል፡፡
ብልጽግና ፓርቲ ሰላምና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ የሚያስችሉ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል -የጉባዔው ተሳታፊዎች
Feb 1, 2025 68
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ በሁለተኛ መደበኛ ጉባኤው የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት የሚያረጋግጡና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ የሚያስችሉ ውሳኔዎች እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል ሲሉ የጉባዔው ተሳታፊዎች ገለጹ። ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ በአድዋ ድል መታሰቢያ ከትናንት ጀምሮ እያካሄደ ይገኛል፡፡ ብልጽግና ፓርቲ በመጀመሪያው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወን መቻሉን በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ መክፈቻ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተሳታፊዎች ተናግረዋል። የጉባኤው ተሳታፊ የሆኑት መሰረት መስቀሌ በሰጡት አስተያየት ብልጽግና ፓርቲ በመጀመሪያ ጉባኤው ለህዝብ የገባውን ቃል ወደ ተግባር ቀይሮ ማሳየቱን ተናግረዋል። ፓርቲው የህዝቦችን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ እና የኢትዮጵያን ተደማጭነት ያጎለበቱ በርካታ የዲፕሎማሲ ስራዎችን በማከናወን ውጤት ማስመዝገቡን አንስተዋል። በልማት ስራዎች በተለይም በግብርናው ዘርፍ በተከናው አስደማሚ ተግባራት በሀገሪቱ ተከታታይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅሰዋል። በትምህርት ጥራት ማስጠበቅና በጤና አገልግሎት አሰጣጥ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት መከናወናቸውን ለአብነት አንስተዋል። ሌላው የጉባዔው ተሳታፊ አቶ ንጉሴ ገመዳ በበኩላቸው ከፓርቲው የመጀመሪያ ጉባኤ በኋላ የአድዋ ድል መታሰቢያን ጨምሮ በርካታ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በተለይም በኮሪደር ልማት በአዲስ አበባ ከተማና በክልል ከተሞች እየተከናወነ ያለው ስራ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ገጽታ ከፍ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ተግባሩ ከተሞችን ለኑሮና ለስራ ምቹ እያደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ተሳታፊዎቹ በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ የተጀመሩ የልማት ስራዎች በፍጥነት ተጠናቀው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ የሚያስችሉ ውሳኔዎች ይተላለፋሉ ብለው እንደሚጠብቁም ገልጸዋል። ብልጽግና ፓርቲው በሀገሪቱ እየተከናወኑ ያሉ የሰላምና ልማት ግንባታ ስራዎች የበለጠ ተጠናክረው የሚቀጥሉበትን ውሳኔ እንደሚያሳልፍም እንዲሁ። ከጎረቤት ብሎም ከአለም ሀገራት ጋር ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚጠናከርበትና በኢኮኖሚ የበለጸገች አገር መገንባት የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ብለው እንደሚጠብቁም አንስተዋል። ትናንት የተጀመረው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ እስከ ነገ እንደሚቀጥል መገለጹ ይታወቃል።
ፖለቲካ
የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን አሳልፏል
Feb 1, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ 2 ሺህ 100 ተሳታፊዎች በታደሙበት በደማቅ የመክፈቻ ስነ ስርዓት በትላንትናው ዕለት በይፋ ተጀምሯል። በጉባኤው 1 ሺህ 700 የድምፅ ተሳታፊዎች እንዲሁም የ15 ሀገራት ፓርቲዎች አመራርና ተወካዮችን ጨምሮ 400 የሀገር ውስጥና የውጭ እንግዶች በተጋባዥነት መገኘታቸውም የሚታወቅ ነው። የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ጉባኤውን አስመልክቶ ለኢዜአ በሰጡት መግለጫ ጉባኤው ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ተወካዮችን ባሳተፈና በዴሞክራሲያዊነት እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለትም ጉባኤው መድረኩን የሚመሩ የፕሬዚዲየም አባላትን በመሰየም በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ በስፋት መወያየቱንና አጀንዳዎችን መርምሮ ማጽደቁንም ተናግረዋል። በዚህም የጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት እና የስብሰባ ስነ-ስርዓት ደንብ ላይ በስፋት በመወያየት በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ብለዋል። በመቀጠልም የማዕከላዊ ኮሚቴ እንዲሁም የኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚቴ ሪፖርቶች ለጉባኤው ቀርበው ሰፊ ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ መጽደቃቸውንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ ጉባኤው በፓርቲው የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ነው ያሉት። ከአንደኛ ጉባኤ ማግስት በፓርቲው በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ፈተናዎች እና ፈተናዎችን ለማለፍ የተሔደበትን ርቀት በስፋት መገምገሙንም አንስተዋል። በዚህም የብልፅግና እሳቤ እስከ ታችኛው ህብረተሰብ ክፍል መድረሱ እና እሳቤው ባህል እየሆነ መምጣቱ የተረጋገጠበት ጉባኤ መሆኑን ገልጸዋል። ጉባኤው በነገው ዕለትም ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን የፓርቲ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ጨምሮ የአመራር ምርጫ ይደረጋል ብለዋል። ለዚህም በዛሬው ዕለት አስመራጭ ኮሚቴ በመሰየም የዕለቱ ስብሰባ አሳታፊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ተናግረዋል። ጉባኤው ለመጪዎቹ ዓመታት የሚያገለግሉ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሆነም ጠቁመዋል።
የተርኪዬ ኤኬ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዛፈር ሲራካያ ምን አሉ
Feb 1, 2025 45
  ኢትዮጵያ ከዓለማችን ጥንታዊ ስልጣኔዎች አንዷ ናት። ኢትዮጵያ በአፍሪካ የታሪክ ገጾች ውስጥ ጉልህ ታሪክ የጻፈች እንዲሁም በባህል፣ በታሪክ፣ በብዝሃነት፣ በእምነት፣ በቋንቋና ቅርስ የበለጸገችና በፈተናዎች ሳትበገር ዘመናትን የተሻገረች ሀገር ናት። ተርኪዬና ኢትዮጵያ የነጻነትና ሉዓላዊነት የአይበገሬነት መንፈስ የሚጋሩ ሀገራት ናቸው። ኢትዮጵያ እና ተርኪዬ በታሪክ ጥብቅ ቁርኝነት አላቸው። ተርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር አጠናክራ ትቀጥላለች። ኢትዮጵያ እና ተርኪዬ በዘመናት መካከል የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸው እና ትብብራቸው እያደገ መምጣቱንና በርካታ ስኬቶች እያስመዘገበ ይገኛል። ተርኪዬ ለቀጣናው ሰላምና ልማት መረጋገጥ አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ያነሷቸው ሃሳቦች ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ቀጣናውና የአፍሪካን ብልፅግናን ዕውን ማድረግ የሚያስችሉ ናቸው።
የካዛኪስታን የታችኛው ምክር ቤት እና የገዢው አማናት ፓርቲ አባል ሳማት ኑርታዛ ምን አሉ
Feb 1, 2025 57
  ኢትዮጵያ ለካዛኪስታን ታማኝ እና እውነተኛ አጋር ናት። ከኢትዮጵያ ጋር የሁለትዮሽ፣ የባለብዝሃ ወገን እና ሁሉን አቀፍ ትብብሯን ለማጠናከር ትሻለች። ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ለቀጣናው እና ዓለም አቀፍ ደህንነት ቁልፍ አበርክቶ አድርጋለች። የብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፍቷል። ብልጽግና ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ረገድ ስኬታማ ተግባር አከናውኗል። አማናት ፓርቲ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ያለውን ግንኙነት እና ካዛኪስታን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር ለማጎልበት ይሰራል። አማናት ለዓለም ሰላም እና ብልጽግና ከብልጽግና ፓርቲ ጋር በትብብር መስራት ይሻል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር ሰጪነት ብልጽግና ፓርቲ የለውጥ እና የሽግግር ተምሳሌት መሆን ችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፖለቲካ ቁርጠኝነት እና ባለ ራዕይ መሪነት፤ ውጤታማ አስተዳደር ሀገርን ከቀውስ በማውጣት ለዘላቂ ልማት መሰረት መጣል እንደሚቻል በግልጽ ያመላከተ ነው።
የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ለብልጽግና ፓርቲ 2ኛ ጉባዔ የመልካም ምኞት መልዕክት ላከ
Feb 1, 2025 70
አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2017(ኢዜአ)፦የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ለብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ የድጋፍና የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፏል፡፡ ኢትዮጵያ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት እያስመዘገበችው ላለው ሁለንተናዊ እድገት የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ (CPC) ያለውን አድናቆት ገልጿል። ቻይና የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጦ ብልጽግና ፓርቲ ኢትዮጵያ ተስማሚ የሆነ የእድገትና የዘመናዊነት መንገድ እንድትከተል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ጠቅሷል፡፡ ለአብነትም በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ የዜጎችን ኑሮ በማሻሻል፣ በአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ ዘላቂ የአካባቢ ጥበቃን በማሳደግ፣ የሀገራዊ ምክክር ቅድመ-ዝግጅት በማገባደድና ማህበራዊ አንድነትን በማጎልበት ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶች ጉልህ መሀኖቸውን ጠቅሷል። እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያን “የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት” እንድትሆን እያስቻሉ ነው ሲልም እውቅና ሰጥቷል፡፡ በቀጣይ ዓመታት ብልጽግና ፓርቲ ሀገሪቱን ወደ “አዲስና የላቀ ስኬት” መምራቱን እንደሚቀጥል ያለውን እምነት ገልጿል፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ላለው ጥልቅ ትብብር አጽንኦት በመስጠትም የሁለቱ ፓርቲዎች መሪዎች ከዚህ ቀደም የደረሱባቸውን ስምምነቶች ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝቧል፡፡ በቀጣይ የቻይናን እና የኢትዮጵያን ትብብር በሁሉም ዘርፎች በማስፋት በማንኛውም ሁኔታ የማይናወጥ ስትራቴጂያዊ አጋርነት ሆኖ የበለጠ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርቧል። ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ የኢትዮጵያን ቀጣይ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ፍኖተ ካርታ የሚቀርፅበት ወሳኝ ሁነት እንደሆነ እና ለሀገራዊ ልማት ወሳኝ የሆኑ ቀጣይ ግቦችን እንደሚቀመጡ እምነት እንዳለው በመጥቀስ ለጉባኤው ስኬት መልካሙን ሁሉ ተመኝቷል፡፡
ብልጽግና ፓርቲ ሰላምና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ የሚያስችሉ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል -የጉባዔው ተሳታፊዎች
Feb 1, 2025 68
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ በሁለተኛ መደበኛ ጉባኤው የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት የሚያረጋግጡና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ የሚያስችሉ ውሳኔዎች እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል ሲሉ የጉባዔው ተሳታፊዎች ገለጹ። ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ በአድዋ ድል መታሰቢያ ከትናንት ጀምሮ እያካሄደ ይገኛል፡፡ ብልጽግና ፓርቲ በመጀመሪያው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወን መቻሉን በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ መክፈቻ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተሳታፊዎች ተናግረዋል። የጉባኤው ተሳታፊ የሆኑት መሰረት መስቀሌ በሰጡት አስተያየት ብልጽግና ፓርቲ በመጀመሪያ ጉባኤው ለህዝብ የገባውን ቃል ወደ ተግባር ቀይሮ ማሳየቱን ተናግረዋል። ፓርቲው የህዝቦችን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ እና የኢትዮጵያን ተደማጭነት ያጎለበቱ በርካታ የዲፕሎማሲ ስራዎችን በማከናወን ውጤት ማስመዝገቡን አንስተዋል። በልማት ስራዎች በተለይም በግብርናው ዘርፍ በተከናው አስደማሚ ተግባራት በሀገሪቱ ተከታታይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅሰዋል። በትምህርት ጥራት ማስጠበቅና በጤና አገልግሎት አሰጣጥ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት መከናወናቸውን ለአብነት አንስተዋል። ሌላው የጉባዔው ተሳታፊ አቶ ንጉሴ ገመዳ በበኩላቸው ከፓርቲው የመጀመሪያ ጉባኤ በኋላ የአድዋ ድል መታሰቢያን ጨምሮ በርካታ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በተለይም በኮሪደር ልማት በአዲስ አበባ ከተማና በክልል ከተሞች እየተከናወነ ያለው ስራ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ገጽታ ከፍ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ተግባሩ ከተሞችን ለኑሮና ለስራ ምቹ እያደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ተሳታፊዎቹ በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ የተጀመሩ የልማት ስራዎች በፍጥነት ተጠናቀው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ የሚያስችሉ ውሳኔዎች ይተላለፋሉ ብለው እንደሚጠብቁም ገልጸዋል። ብልጽግና ፓርቲው በሀገሪቱ እየተከናወኑ ያሉ የሰላምና ልማት ግንባታ ስራዎች የበለጠ ተጠናክረው የሚቀጥሉበትን ውሳኔ እንደሚያሳልፍም እንዲሁ። ከጎረቤት ብሎም ከአለም ሀገራት ጋር ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚጠናከርበትና በኢኮኖሚ የበለጸገች አገር መገንባት የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ብለው እንደሚጠብቁም አንስተዋል። ትናንት የተጀመረው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ እስከ ነገ እንደሚቀጥል መገለጹ ይታወቃል።
ማህበራዊ
ሆስፒታሉ የህክምና መገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አገኘ
Feb 1, 2025 55
መቀሌ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦ በትግራይ ክልል የዓይደር ሰፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል 96 ሺህ ዶላር የሚገመት የህክምና መገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገለት። ሆስፒታሉ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ያገኘው ስዊድን ከሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መሆኑ ታውቋል። ትውልደ ኢትዮጵያዊያኑን ወክለው በዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል ተገኝተው ቁሳቁሱን ያስረከቡት አቶ አርአያ ገብረእግዚአብሔር እንደገለጹት፤ በ96 ሺህ ዶላር ተገዝተው በድጋፍ ከተሰጡ የህክምና መሳሪያዎች መካከል ስድስት የኩላሊት ማጠቢያ (የድያሊስስ ) ማሽኖች፤ አንድ አልትራ ሳውንድ እና ህሙማን ለማመላለስ የሚያገለግሉ የአካል መደገፊያዎች ይገኙበታል። በቀጣይም ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ለሆስፒታሉ ተጨማሪ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችን እየገዙ ለመላክ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የህክምና መገልገያ መሳሪያዎቹን ድጋፍ የተረከቡት የዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር አብርሃ ገብረእግዚአብሔር በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ የተሰጡን የህክምና መሳሪያዎች ህሙማንን የተሻለ የምርመራ አገልግሎት እንዲያገኙት ይረዳቸዋል። የሆስፒታሉን የህክምና መገልገያ ቁሳቁስ ችግር ለመፍታት የሃብትና የሃሳብ ድጋፍ እያደረጉ ላሉ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን አመስግነዋል። በአገር ውስጥና በውጭ ሚገኙ የክልሉ ተወላጆች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና ሌሎች አካላትም ሆስፒታሉ ያለበትን ከፍተኛ የመድሃኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች ችግር ተገንዝበው ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
ፕሮግራሙ የህብረተሰቡ ኑሮ እንዲሻሻል ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Feb 1, 2025 53
ደሴ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦ የምግብ ዋስትና ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ኑሮ እንዲሻሻል ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በደሴ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሽመልስ ጌታቸው ገለጹ። ሁለተኛ ምዕራፍ የመጀመሪያው ዙር የከተሞች ልማታዊ ሴፍትኔትና ስራ ፕሮጀክት የኑሮ ማሻሻያ ማጠቃለያና ሌላ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ዛሬ በደሴ ከተማ ተካሂዷል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባው በወቅቱ እንደተናገሩት፤ በፕሮግራሙ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በከተማው የመንገድ፣ የጽዳት፣ አረንጓዴ ልማትና የጎርፍ መከላከል ተግባራትን በማከናወን ተጨባጭ ውጤቶች ማስመዝገብ ተችሏል፡፡ የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ኑሮ እንዲሻሻል፣ የሥራ ባህላቸው እንዲጎለብትና ሀብት ማፍራት እንዲጀምሩ ምቹ መደላድል መፍጠር እንደቻለ ገልጸዋል፡፡ በአዲስ ወደ ፕሮግራሙ የሚቀላቀሉ ከበፊት ተጠቃሚዎች ልምድ በመውሰድ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆኑና በከተማው ልማት ላይ አሻራቸውን እንዲሳርፉ ይደረጋል ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ ምግብ ዋስትናና ሴፍትኔት ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ሙሴ በበኩላቸው፤ በሁለተኛው ምዕራፍ የመጀመሪያው ዙር ፕሮጀክት 60 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ አንድ ሺህ 440 አባ ወራና እማወራዎች ሦስት ዓመታት በተለያዩ የልማት ሥራዎች በማሳተፍ ተጠቃሚ እንደሆኑ ጠቅሰዋል። ተመራቂዎቹ በእንሰሳት ማድለብ፣ በአገልግሎትና በሌሎችም የሥራ ዘርፎች የግል ስራ መጀመራቸውን አመልክተው፤ ኑሯቸው ከመሻሻሉ ባለፈ ሀብት መፍራትና ለሌሎችም የሥራ ዕድል መፍጠር የጀመሩም መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በሌላ ፕሮግራም ከ6 ሺህ 800 የሚበልጡ ሰዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የማስጀመሪያ መረሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።
በሐረሪ ክልል ከ14 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ
Feb 1, 2025 53
ሐረር፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ከ14 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ መያዙን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ጣሰው ቻለው እንደገለጹት የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-06153 ድሬ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ የጫነው የኮንትሮባንድ እቃ ጭኖ ከተደበቀበት ስፍራ በህብረተሰቡ ጥቆማ ተይዟል። ተሽከርካሪው ትናንት ሌሊት 10 ሰዓት በሐረር ከተማ በተለምዶ ሜንሽን በሚባለው አካባቢ በሚገኙ ጅምር የቤቶች ግንባታ ውስጥ ተሸሽጎ መገኘቱንም ገልጸዋል። የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ከ14 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው የተለያዩ የሲጋራ ምርቶች እንደሆኑ ተናግረዋል። በቁጥጥር ስር የዋለው የኮንትሮባንድ ዕቃ ለሐረር ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ገቢ መደረጉንም ጠቁመው ፖሊስ አሽከርካሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል በክትትል ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ኮንትሮባንድ የሀገር ኢኮኖሚ የሚጎዳ በመሆኑ በመከላከሉ ረገድ ህብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር እየሰጠ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ኮማንደር ጣሰው አሳስበዋል።
በመዲናዋ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር ሁለት ነጥብ አምስት ሚሊየን ደርሷል
Feb 1, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ የጤና አገልግሎቱን ፍትሃዊነት ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚዎችን ቁጥር 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ማድረስ መቻሉን የከተማዋ ጤና ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ኃላፊ ዶክተር ዮሃንስ ጫላ ለኢዜአ እንዳሉት የጤና አገልግሎት ስራውን ተደራሽነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ ነው። ባለፉት ስድስት ወራትም የጤና የአገልግሎቱን ተደራሽነት ይበልጥ ለማስፋት በተከናወኑ ተግባራት በከተማዋ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በዚህም የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት ተጠቃሚነት አምና ከነበረው 2 ነጥብ 3 ሚሊየን ወደ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል። ቢሮ ኃላፊው ከተማ አስተዳደሩ ለማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ድጎማ ማድረጉንም ገልጸዋል። ተደራሸነቱን ለማረጋገጥ ጤና ጣቢያ በሌለባቸው ስድስት ወረዳዎች ላይ የጤና ጣቢያ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን አንስተው የአዳዲስ ሆስፒታሎች ግንባታ እና የነባር ሆስፒታሎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ የማስፋፊያ ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣ ጀሞ እና በኮልፌ ቀራኒዮ መንዲዳ አካባቢዎች የሆስፒታል ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው በዘውዲቱ፣ ራስ ደስታና ሌሎችም ሆስፒታሎች ደግሞ የማስፋፊያ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። ዶክተር ዮሃንስ ጫላ እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት 7 ነጥብ 8 ሚሊዮን ታካሚዎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት አግኝተዋል። ባለፉት ስድስት ወራት ለ700 ሺህ በላይ ህፃናት የፖሊዮ ክትባት መሰጠቱን ገልጸው ለታዳጊ ሴቶች የማህፀን በር ካንሰር ክትባትን በስፋት ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል። በተጨማሪም በ11 ጤና ተቋማት የዲጂታል መረጃ አያያዝ ስርዓት ውስጥ እንዲገቡ መደረጉን ጠቅሰው፤ በዚህም የዲጂታል አገልግሎት የሚሰጡ ጤና ተቋማትን ቁጥር ወደ 51 ማሳደግ መቻሉንም ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያስመዘገበች ያለው ውጤት ለአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚያደርጋት ነው- የቱሪዝም ሚኒስቴር
Feb 1, 2025 61
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያስመዘገበች ያለው ውጤት ለአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚያደርጋት መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። የሀገሪቱን እድገት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንዲያስችሉ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ካሉ ዘርፎች መካከል ቱሪዝም አንዱ ነው። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ከለውጡ ወዲህ መንግስት ለቱሪዝም ልማት በተሰጠው ተኩረት በርካታ የቱሪዝም መሰረተ ልማቶች ተገንብተዋል። በአዲስ አበባ የተጀመረው ገበታ ለሸገር ፕሮጀክትን ጨምሮ የገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶችን ለአብነት አንስተዋል። በተጨማሪም ነባር የቱሪስት መዳረሻዎችን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በፍጥነት በማደስ ለጎብኚዎች ክፍት የማድረግ ስራም በትኩረት መከናወኑን አስታውቀዋል። በቱሪዝም ልማት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት ኢትዮጵያን ለአፍሪካ ሀገራትም ጭምር ምሳሌ የሚያደርጋት መሆኑን አመልክተዋል። ለዚህም የኢጋድ አባል ሀገራት የሚመሩበት የዘላቂ ቱሪዝም ማስተር ፕላን አዲሰ አበባ ላይ ይፋ መደረጉ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ከዚህም በተጨማሪ ዘርፉ የታለመለትን አገራዊ ስኬት የበለጠ እንዲያስመዘግብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሪፎርምና መሰል የማሻሻያ ስራዎችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው አስታውቀዋል፡፡ ላለፉት 15 ዓመታት ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የቱሪዝም ፖሊሲን የመከለስ ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቅርቡም አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ ይፋ የሚደረግ መሆኑን ጠቁመዋል።
አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ በክልሉ በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎችን ያጠናክራል - አቶ ጌታቸው ረዳ
Feb 1, 2025 67
መቀሌ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦ አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ በክልሉ በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎችን ለማጠናከርና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማጎልበት እንደሚያግዝ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ ገለጹ። አዲሱን የግብርናና የገጠር ልማት ፖሊሲ በዘርፉ ለተሰማሩ ባለድርሻ አካላት የማስተዋወቅ መርሀ ግብር ዛሬ በመቀሌ ከተማ ተካሂዷል። በዚሁ ጊዜ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ፤ ፖሊሲው በክልሉ በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎችን ለማጠናከርና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ያግዛል ብለዋል።   ግብርናን ማዘመን ምርታማነትን ለማጎልበት የሚያግዙ ስራዎችን ማከናወንና ሜካናይዜሽን ላይ ማተኮር መሆኑን ጠቅሰዋል። ፖሊሲው የክልሉን እርሻ ለማጎልበት የሚደረገውን ጥረት ስለሚያጠናክር ለተግባራዊነቱ ባለድርሻ አካላት የተለየ ትኩረት ሊሰጡበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በግብርና ሚኒስቴር የፖሊሲ ምርምርና ጥናት መሪ ስራ አስፈፃሚ ተስፋዬ መንግስቴ(ዶ/ር) በበኩላቸው በግብርናው ዘርፍ ውጤታማ ለውጦችን ለማምጣት የግብርና ኮሜርሻላይዜሽንን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። በግብርና ዘርፍ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የፖሊሲና የስርዓተ ምግብ ዳይሬክተር አቶ ረታ ዋጋሪ፤ ፖሊሲው ተግባራዊ በሚደረግበት ወቅት የባለድርሻ ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ መድረኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።   ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ብርሀነ ሀይለ የተባሉ የግብርና ባለሙያ፤ በግብርናው ዘርፍ እየታዩ ያሉት ዘርፈ ብዙ ለውጦችን ይበልጥ ለማጎልበት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ማጎልበት ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ዘርፍ የምርምር ስራ ላይ የተሰማሩት አባዲ ግርማይ(ዶ/ር) ደግሞ፤ የግብርና ዘርፍ ለኢኮኖሚው እድገት ያለው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ የተለየ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አመልክተዋል። ፖሊሲው ለሀገሪቱ ዘላቂ ልማት ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ ለተግባራዊነቱም የሁሉም አካላት ቅንጅታዊ ስራ አስፈላጊ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የማህበራዊ ልማት ዘርፍ ሽግግር ሀላፊ ሴክሬታሪያት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት ናቸው።
በግማሽ ዓመቱ ከ12 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል - የክልሉ ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን
Feb 1, 2025 58
ዲላ፤ ጥር 24/2017 (ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በግማሽ ዓመቱ ከ12 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ የግማሽ አመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በዲላ ከተማ አካሂዷል። የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሪክተር አቶ አማኑኤል ብሩ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ በግማሽ ዓመት ከ12 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል። በክልሉ ከ134 ሺህ ቶን በላይ እሸት ቡና ተሰብስቦ የደረቅ ቡና ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው በምርት ዘመኑ ተሰብስቦ የተከማቸ ቡናን በቀጣይ ሶስት ወራት አሟጦ ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ህገወጥ የቡና ዝውውርን ከመቆጣጠር በተጓዳኝ አቅራቢዎች ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ እንዲያቀርቡ በየደረጃው ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን አንሰተዋል። በዞኑ በግማሽ አመት ከ10 ሺህ ቶን በላይ ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን ያነሱት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ቡናና ቅመማ ቅመም ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ኤርሚያስ ቼካ ናቸው። በምርት ዘመኑም ከ200 በላይ ቡና አምራቾች ከ17 ሺህ ቶን በላይ የታጠበ ቡና ማዘጋጀት መቻላቸውን ጠቅሰው ይህንንም በቀጣይ ወራት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው ብለዋል። ይህም በበጀት ዓመቱ ከ28 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል።
በሐረሪ ክልል የተከናወነው የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት የቱሪስት ፍሰት እንዲጨመር አስችሏል- አቶ ተወለዳ አብዶሽ
Feb 1, 2025 55
አዲስ አበባ ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል የተከናወነው የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት የቱሪስት ፍሰት እንዲጨመር ማስቻሉን የክልሉ ባህል ቅርስ እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወለዳ አብዶሽ ገለጹ። ኃላፊው በሰጡት መግለጫ ከለወጡ ወዲህ በክልሉ የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት ከጁገል ዓለም አቀፉ ቅርስ መልሶ ልማት ጀምሮ የጅብ ትርዒት ማሳያ ፓርክ ግንባታዎች በዋናነት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በክልሉ የተከናወኑ የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት እና እድሳት ኢንሼቲቮች የመዳረሻዎችን ህልውና ከማስጠበቅ ባለፈ የቱሪስት ፍሰቱን እንዲጨምር ያስቻሉ መሆናቸውን አመልክተዋል። የውጪና የሃገር ውስጥ ጎብኚዎች በክልሉ መበራከታቸውንን ለአብነት አንስተዋል። በተያዘው አመት ብቻ 4 ሺህ 991 የውጭ አገር ጎብኚዎች ወደ ክልሉ መምጣታቸውን የገለፁት አቶ ተወለዳ የቱሪስት ፍሰቱ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ37 በመቶ እድገት ማሳየቱን ጠቁመዋል። 92 ሺ 581 የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች በክልሉ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችን መጎብኘታቸውንም ተናግረዋል። በኮሪደር ልማት የተፈጠሩ ምቹ የእግረኛ መንገዶች እና የአረንጓዴ ልማቶች ለቱሪስት ፍሰቱ ምቹ ሁኔታን ፈጥረዋል ነው ያሉት። በክልሉ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ይበልጥ በማጎልበት የቱሪስተ ፍሰት እና ቆይታን ለማሳደግ የቱሪዝም ዘርፉ የሚፈልገውን የመሠረተ ልማቶች እና የሆቴል ቱሪዝም የማጠናከር ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በሌላ በኩል በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የኢኮ ፓርክን በሙሉ አቅሙ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ሐረር የምትታወቅባቸውን የአብሮነት እሴቶችን ጠብቆ ለማቆየት የተለያዩ ህዝባዊ በዓላትና ሁነቶችን ወንድማማችነትን ይበልጥ አጉልቶ በሚያሳይ መልኩ መከበራቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አየር ኃይል አሁን ለገነባው ከፍተኛ ወታደራዊ የዝግጁነት አቅም የሙያተኛው ድርሻ የጎላ ነው - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
Feb 1, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦አየር ኃይል አሁን ለገነባው ከፍተኛ ወታደራዊ የዝግጁነት አቅም የሙያተኛው ድርሻ የጎላ መሆኑን የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ። የኢፌዴሪ አየር ኃይል ሎጀስቲክስ የእውቅና እና የምስጋና መርሃ-ግብር በአየር ኃይል መኮንኖች ክበብ አካሂዷል። ዋና አዛዡ በመርሃ-ግብሩ በመገኘት ለተቋሙ የግዳጅ አፈፃፀም ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ክፍሎች የእውቅና እና የምስጋና ሰርተፍኬት ሰጥተዋል። ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የአየር ኃይል ሎጀስቲክስ የተቋሙን የማድረግ አቅም ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገሩ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን ጠቅሰው አየር ኃይሉ ለገነባው አሁናዊ ከፍተኛ የዝግጁነት አቅም የክፍሉ ሙያተኞች ድርሻ ከፍተኛ እንደነበረ ተናግረዋል ። የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር ሎጀስቲክስ ብርጋዲየር ጄኔራል ነገራ ሌሊሳ በበኩላቸው ተቋሙ አዳዲስ የአቪዬሽን ትጥቆችን ከመታጠቅ ባለፈ ያሉትን ጠግኖ ወደ ግዳጅ በማሰማራት ረገድ ክፍሉ ያከናወነው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይነትም በሁሉም መስክ የጀመርናቸውን ስራዎች በላቀ የስራ ተነሳሽነት አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተሰጣቸውን ግዳጅ እና ተልዕኮ በብቃት ከመፈፀም ባለፈ ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን ለሰሩ ክፍሎች የእውቅና እና የምስጋና ሰርተፊኬት እንደተሰጣቸው ከመከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በክልሉ ልማትን የሚያጠናክሩ መረጃዎች ተደራሽ በማድረግ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚያጎለብቱ ተግባራት ይቀጥላሉ
Feb 1, 2025 51
ቦንጋ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የወል በሆነ መልኩ ልማትና ዕድገትን የሚያጠናክሩ መረጃዎች ተደራሽ በማድረግ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚያጎለብቱ ተግባራት እንደሚቀጥሉ የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ገለጸ። የቢሮው የበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የተግባር አፈጻጸም ላይ የመከረ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሄዷል። በዚህ ወቅት የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ፣ ቢሮው የመረጃ ተደራሽነትን ለማስፋት የመገናኛ ብዙሃን እና የኮሙኒኬሽን መዋቅሩን በማስተባበር በርካታ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል። ለአብነት ክልሉ ያሉ የልማት አቅሞች በማስተዋወቅ በኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝምና በሌሎች ሀብቶች እንዲመጡና ማህበረሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረጉን ጠቅሰዋል። እንደአገር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመቻቹ የተለያዩ ኢንሼቲቮችን ለህዝብ ለማስተዋወቅና ሀሳቡን ለማስረፅ በተከናወነው ስራ ተስፋ ሰጪ ለውጥ መምጣቱንም ጠቁመዋል። በተለይም የወል በሆነ መልኩ ዕድገትንና ልማትን የሚያጠናክሩ መረጃዎች ተደራሽ በማድረግ ረገድ ከመገናኛ ብዙሃን ጋር በመተባበር በተደረገው ጥረት የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚያጎልበቱ ተግባራት እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። በቀጣይም በዋና ዋና የልማት አጀንዳዎች፣ ሰላምን በሚገነቡና የሕዝቦች ትስስርን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ በተቀናጀ መንገድ እንደሚሰራመ አቶ የሺዋስ አብራርተዋል። በመድረኩ የተሳተፉ የመገናኛ ብዙሃንና የኮሙዩኒኬሽን አመራር አባላት በሰጡት አስተያየት፤ከለዉጡ ወዲህ መንግስት ያመቻቸውን የመገናኛ ብዙሃን ነፃነት በመጠቀም በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። በቀጣይም የአገሪቱ የልማትና ብልፅግና ጉዛ የተሳካ እንዲሆን ህብረተሰቡን በማንቃትና እውነታውን በማሳወቁ ረገድ የሚጠበቅባቸውን አንደሚወጡ ገልጸዋል። ለአንድ ቀን በተካሄደው የምክክር መድረኩ የተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ተወካዮች፣ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የኮሙዩኒኬሽን ሥራ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የጥናትና ምርምር ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግና ችግሮችን ለመፍታት አቅም መሆን አለባቸው
Jan 31, 2025 72
ሀዋሳ ፤ጥር 23/2017 (ኢዜአ):- በምሁራን የሚሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግና ችግሮችን ለመፍታት አቅም ከመሆን ባለፈ መንግስት ለሚነድፋቸው ፖሊሲዎች ግብዓት መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር "ብሔራዊ ጥቅሞቻችንና ቀጣናዊ ትስስር ለሚዛናዊ የህዝቦች ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሄዷል።   በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጪ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ ጅሀድ ናስር እንደገለፁት፤ በዩኒቨርሲቲ ምሁራን የሚያደርጉት የጥናትና ምርምር ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግና ችግሮችን ለመፍታት አቅም ከመሆን ባለፈ መንግስት ለሚነድፋቸው ፖሊሲዎች ግብዓት ሊሆኑ ይገባል።   በውይይት መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴርን በመወከል የተገኙት በተቋሙ የብሔራዊ መግባባት ባለሙያ ወይዘሮ ሲሳይ ብርሌ እንዳሉት ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅና ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት የምሁራን ሚና የላቀ ነው። የዛሬው ውይይትም ለሀገር እድገት ግብዓት የሚሆኑ የጥናት ውጤቶችንና አማራጭ ሀሳቦችን ምሁራን የሚያፈልቁበት አጋጣሚን የማመቻቸት ዓላማ እንዳለውና መሰል መድረኮችም በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚካሄዱ ተናግረዋል።   የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ችሮታው አየለ (ዶ/ር) እንዳሉት ምሁራን ሀገርና ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የምርምር ስራዎችን መስራት ይጠበቅባቸዋል። መድረኩ ምሁራን ለቀጣናዊ ትስስሮችና ለሀገር ግንባታ ያላቸውን አበርክቶ ለማጉላት የዳበረ ምክረ ሀሳብ ማቅረብ እንዲችሉ ታስቦ መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል። በዩኒቨርሲቲው የማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ተመራማሪ ዳኜ ሽብሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት በኢትዮጵያ ሰላምን፣ ልማትንና ብልጽግናን ለማምጣት ከቀጣናው ሀገራት ጋር ተባብሮና ተደጋግፎ መስራት ያስፈልጋል።   የኢትዮጵያ ሰላም ለቀጣናው ሰላምና ልማት መጠናከር የላቀ ሚና ስላለው ለተግባራዊነቱም ቀጣናዊ ትብብር ላይ መስራት የግድ እንደሚል ተናግረዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴርና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተወካዮችና የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።
11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል
Jan 31, 2025 72
  አዲስ አበባ፤ጥር 23/2017(ኢዜአ)፦ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የወሰዱ ዜጎች ቁጥር 11 ነጥብ 5 ሚሊዮን መድረሱን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል፡፡ የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ የነዋሪዎችን የባዮሜትሪክ (የጣት አሻራ፣ የአይን አይሪስ እና የፊት ምስል) እንዲሁም የግል መረጃዎችን በመሰብሰብ አንድን ግለሰብ ልዩ በሆነ መልኩ እንዲታወቅ የሚያስችል ነው፡፡ ይህም ዘመናዊ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓትን በመገንባት ማንነትን የማረጋገጥ ሂደት ቀልጣፋ እና ደህንነቱ የተረጋገጠ እንዲሆን ያደርጋል። የፕሮግራሙ የስትራቴጂክ የኮሙኒኬሽን አማካሪ አቶ አቤኔዘር ፈለቀ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ፕሮግራሙ ከተጀመረ አመታት ማስቆጠሩን ተናግረዋል። በነዚህ አመታት ውስን በፕሮግራሙ የታቀዱ ውጥኖች ማሳካት የሚያስችሉ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል።   እስከ አሁን ድረስ ከ1 ሺህ በላይ በሆኑ የምዝገባ ጣቢያዎች 11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች መታወቂያውን መውሰዳቸውን አስታውቀዋል። ከ52 ተቋማት ጋር ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ትግበራና የአሰራር ትስስር መዘርጋት የሚያስችል ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን 12 የሚደርሱ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንደ ቅድመ ሁኔታ በማስቀመጥ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙም ገልጸዋል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የሕግና ፖሊሲ ክፍል ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም በበኩላቸው፥ በ2017 ዓ.ም የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ በተጠናከረ አግባብ እየተከናወነ ነው ብለዋል። በዚህም በተቋሙና በምዝገባ ሂደት አጋር በሆነው ኢትዮ ቴሌኮም አማካኝነት በአገር አቀፍ ደረጃ ምዝገባ እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል።   ይህም በከተሞች ብቻ የነበረውን ምዝገባ በገጠር አካባቢዎችም ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰው፥ ይህም በዓመቱ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት እንደሚያስችል ጠቅሰዋል። ምዝገባውን በድንበር አካባቢዎችም ተደራሽ ለማድረግ በግል ተቋማት የሚከናወን ሱፐርኤጀንት የሚባል አሰራር ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቁመዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተግባራዊ መደረጉ ሁሉን አቀፍ፣አካታችና አስተማማኝ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችልም ተመላክቷል። ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ዘርፈ ብዙ አስፈላጊነትን በመገንዘብ በአቅራቢያቸው በሚገኙ የመመዝገቢያ ጣቢያዎች በመመዝገብ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ እንዲሆኑም ኃላፊዎቹ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ስፖርት
በገንዳ ውኃ ከተማ  ለወጣቶች ምቹ የስፖርት ማዘውተሪያ  የማልማት ስራ እየተከናወነ ነው
Feb 1, 2025 73
ገንዳ ውኃ ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውኃ ከተማ ለወጣቶች ምቹ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን የማልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማው አስተዳደር ገለጸ። በከተማው ሰባት የአዋቂዎች እግር ኳስ ቡድኖች የሚሳተፉበት ውድድር ዛሬ ተጀምሯል። የገንዳ ውኃ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ አብዱልከሪም ሙሀመድ ውድድሩ ሲጀመር ባደረጉት ንግግር ፤ ስፖርት ሰላም፣ ልማትና አንድነትን የሚያጠናክር እሴት ነው ብለዋል። ስፖርት ለሰላም፤ ለልማትና ለጤና መሆኑን የሚገነዘብ ወጣት ከማፍራት ባሻገር ለወጣቶች ምቹ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን የማልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በከተማው ሀያ ስድስት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መለየታቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህም ስድስት የሚሆኑትን የማልማት ስራ እየተካሄደ መሆኑንና ይሄው ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረኪዳን መንጋው በበኩላቸው፤ የስፖርት ዘርፉን በማጠናከር ጤናማ፤ ለሰላምና ልማት የሚተጋ ትውልድ የመፍጠር ተግባር እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። "ስፖርት ፍቅርና አንድነትን የምናጠናክርበት መስተጋብራችን ነው" ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ የህዝብ ግንኙነት አማካሪ አቶ ልዑልሰገድ አሰፋ ናቸው። የሰላም መገለጫ የሆነውን ስፖርት በማዘመን ወጣቶች ለአካባቢያቸው ብሎም ለአገራቸው ሰላምና ልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ ማድረግ እንደሚጠበቅም ገልጸዋል። በከተማው ሰባት የአዋቂዎች እግር ኳስ ቡድኖች የሚሳተፉበት ውድድሩ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ግንቦት 30/2017 ዓ.ም እንደሚቆይ ተመልክቷል።
አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ ለተጫዋቾች ጥሪ አደረጉ 
Feb 1, 2025 62
አዲስ አበባ ፤ጥር 23/2017(ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ ለ16ኛ የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዝግጅት ለ29 ተጫዋቾች ዛሬ ጥሪ አድርገዋል። ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ከነገ ጀምሮ ልምምድ ማድረግ እንደሚጀምሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል። ሉሲዎቹ ከዩጋንዳ ጋር የካቲት 14 እና የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም የደርሶ መልስ ጨዋታ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዩጋንዳ ጋር ለሚያደርገው የማጣሪያ ዝግጅት እንዲረዳ ከጅቡቲ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ጋር የካቲት 5 እና የካቲት 9 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም የአቋም መለኪያ ጨዋታ እንደሚያካሂድ ታውቋል። በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው 16ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ መርሃ ግብሩ በሁለት ዙር እንደሚከናወን እና 38 ሀገራት እንደሚሳተፉ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስታውቋል። ኢትዮጵያ ዩጋንዳን በደርሶ መልስ ካሸነፈች በሁለተኛው ዙር ከታንዛንያ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። 11 ሀገራት ከአዘጋጇ ሞሮኮ ውጪ በአህጉራዊው መድረክ ለመሳተፍ ይፋለማሉ። በአፍሪካ ዋንጫ ላይ 12 ሀገራት ይሳተፋሉ።
ፋሲል ከነማ ወደ ድል ተመልሷል 
Jan 31, 2025 77
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2017 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሃ ግብር ፋሲል ከነማ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሀብታሙ ተከስተ እና አንዋር ሙራድ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ሙኸዲን ሙሳ ለድሬዳዋ ከተማ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ ፋሲል ከነማ በሊጉ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል። በ20 ነጥብ ደረጃውን ከ14ኛ ወደ 9ኛ ከፍ አድርጓል። ቡድኑ በውድድር ዓመቱ አራተኛ ድሉን አሳክቷል። በአንጻሩ በሊጉ አራተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ19 ነጥብ ከ10ኛ ደረጃ 11ኛ ዝቅ ብሏል። ድሬዳዋ የዛሬውን ጨምሮ ባለፉት ስድስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ቀን ላይ በተደረገ ጨዋታ የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ መድን ሀዲያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የ17ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የ18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳሉ። ኢትዮጵያ መድን ሊጉን በ32 ነጥብ እየመራ ነው። ቅዱስ ጊዮርጊስ በ28 እና መቻል በ27 ነጥብ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። አዳማ ከተማ፣ ሃዋሳ ከተማ፣ ስሑል ሽሬ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ15ኛ እስከ 18ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የተፋሰስ ልማት የግብርና ልማት ስራቸውን ያቃናላቸው የሁለቱ ዞኖች አርሶ አደሮች
Jan 31, 2025 179
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የልማት አማራጮችን በማስፋት ተጠቃሚነትን እንዳሳደገላቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው የካፋ እና ምዕራብ ሀረርጌ ዞኖች አርዞ አደሮች ገለጹ። በካፋ ዞን ሺሾ-እንዴ ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ወልደየስ ወልደማሪያምና በቀለ ወልደገብርኤል የእርሻ መሬት ለማስፋፋትና በተለያዩ ምክንያቶች የአካባቢ መራቆት በመከሰቱ የግብርና ምርታማነታቸው ቀንሶ እንደነበር አስታውሰዋል። ​ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራዎች ግን የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙና የአፈር ለምነት እንዲመለስ በማስቻላቸው በአትክልፍትፋ ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት መኖ በማልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዕድል ፈጥሮላቸዋል። ​   በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የርዕሰ መስተዳድር የኢኮኖሚና መሰረተ ልማት ዘርፍ አማካሪ (ዶ/ር) ኢንጂነር ምትኩ በድሩ ባለፉት ሦስት ዓመታት በስነ ህይወታዊና አካላዊ ስራዎች የተገኙ አበረታች ውጤቶችን ማስቀጠል ዘንድሮም የተፋሰስ ልማት ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል። በዘንድሮው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ በ1 ሺህ 100 ንዑስ ተፋሰሶች ከ225 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ ተገልጿል። ​ በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጭሮ ወረዳ አርሶ አደሮች በማህበር ተደራጅተው በአካባቢያቸው የሚገኝ ደን በመንከባከብና በመጠበቅ ከእንሰሳት መኖና በንብ ማነብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። ​ አርሶ አደር አቡሌ መሀመድ አሊና ርሶ አደር አደም መሀመድ በማህበር ተደራጅተው በደን ጥበቃና እንክብካቤ ስራዎች በንብ ማነብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረጉን ገልጸው፤ በደን ውስጥ መኖ በማልማት ለእንስሳቶቻቸው በቂ መኖ ማግኘት መቻላቸውን አአረጋገጠዋል። በኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት የሐረርጌ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፋኪያ ጀማል እንዳሉት በምዕራብና ምስራቅ ሀረርጌ ዞኖች በአሳታፊ የደን ጥበቃና እንክብካቤ ከ2 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በ25 ማህበራት ታቅፈው እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ ​ ህብረተሰቡ በባለቤትነት ስሜት ለደን ጥበቃ ማድረግ ከጀመረ ወዲህ በደን ላይ የሚደርስ ጉዳት ቀመቀነሱን ገልጸው ህብረተሰቡ ደኑን በመጠበቅ በውስጡ የእንስሳት መኖ እና ንብ በማነብ እንዲሁም ከደን ውጤቶች ሽያጭ ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ የምዕራብ ሐረርጌ ዞን እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት የሰብል ልማት ስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ መገርሳ ዴሬሳ በዞኑ የግብርና እንሼቲቮችን ተግባራዊ በማድረግ እና ያልታረሱ መሬቶችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተከናወኑት ተግባራት ውጤታማ ሆነዋል በዞኑ 15 ወረዳዎች ለልማቱ ሲውሉ ያልነበሩና በበጋው የተፋሰስ ልማት የአፈር መሸርሸር የሚከላከሉ እርከኖች የተሰሩባቸው መሬቶች ለምነታቸው እየጨመረ በመምጣቱ አርሶ አደሩ ለልማቱ እንዲያውል እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በአጠቃላይ በመኸር ወቅቱ ከ559 ሺህ 343 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የአገዳ፣ ብርዕ እና ቅባት ሰብሎች መልማቱን ገልጸው ይህም ከቀዳሚው አመት ከ159 ሺህ ሄክታር በላይ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል፡፡
በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ ተግባራትን እናከናውናለን-የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች
Jan 30, 2025 74
ሚዛን አማን፤ጥር 22/2017 (ኢዜአ)፦በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እንደሚያከናውኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ። በዞኑ ባሉ ሁሉም መዋቅሮች የዘንድሮ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራ ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። እንደ ዞን በሸይ ቤንች ወረዳ ማዝ ቀበሌ በተጀመረው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ላይ የተሳተፉት አርሶ አደር ታደሰ ኮኒ፥ መሬት ለምነቱን ሲያጣ መርታማነቱ እንደሚቀንስ ገልጸዋል። ይህን ለመከላከል የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችን መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በየዓመቱ እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የተፋሰስ ልማት በተከናወነባቸው አካባቢዎች ሙዝ፣ የመኖ ሣር እና ሌሎች ፍራፍሬዎችን በመትከል ተጠቃሚ ለመሆን ጠንክረው እንደሚሰሩም ጠቅሰዋል። በተፋሰስ በሚለሙ አካባቢዎች የፍራፍሬ ችግኞችን መትከል የተራቆተ ቦታ ፈጥኖ እንዲያገግም ያደርጋል ያሉት ደግሞ አቶ በላይ ወልደየስ የተባሉ አርሶ አደር ናቸው። ከዚህ ቀደም በአካባቢው በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች የተሻለ ለውጥ ማምጣታቸውን ገልጸው፥ በየዓመቱ ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ዘንድሮ የተፋሰስ ልማት በሚሰራባቸው ዳገታማ ቦታዎች ሸንኮራ አገዳና ለአካባቢው ተስማሚ የሆኑ ሌሎች ችግኞችን ለመትከል መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል። በተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራው በግብርና ባለሙያዎች ምክረሀሳብ መሰረት ምርታማነትን የሚጨምሩና ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችሉ የግብርና ሥራዎችን መሥራት ከሁላችንም ይጠበቃል ወይዘሮ ጣይቱ ሙሉጌታ የተባሉ ሌላዋ የተፋሰስ ልማት ሥራው ተሳታፊ ናቸው። የቤንች ሸኮ ዞን ግብርና፣አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ በዞኑ በ34 ሺህ 480 ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ተግባር እንደሚከናወን ገልጸዋል። ለዚህም በ96 ንዑስ ተፋሰሶች ላይ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ዛሬ በሁሉም መዋቅሮች ወደ ተግባር ተገብቷል ብለዋል። በለሙ ተፋሰሶች የፍራፍሬ ችግኝ በስፋት በመትከል አርሶ አደሩ ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆን መምሪያው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም አስገንዝበዋል። የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን መንገሻ የተፋሰስ ልማቱን በይፋ ሲያስጀምሩ እንደገለጹት፣የተፈጥሮ ሀብትን መጠበቅ ሰውና እንስሳትን ይበልጥ ተጠቃሚ የሚያድርግ ነው። የመሬት ለምነትን ለመጠበቅና የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው የተቀናጀ አፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በክልሉ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወነው የተፈጥሮ ሀብት ልማት ስራ የደን ሽፋኑን ከማሳደግ አንጻር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል - የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ
Jan 30, 2025 74
አዳማ፤ ጥር 22/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወነው የተፈጥሮ ሀብት ልማት ስራ የደን ሽፋኑን ከማሳደግ አንጻር ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ዘርፍ ምክትል ሃላፊ አቶ ኢሊያስ ከድር ለኢዜአ እንደገለጹት የተፈጥሮ ሀብትን በማልማት ለትውልድ ለማስተላፍ እየተሰራ ነው። በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት የክልሉ የተፋሰስና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ስራዎች ለግብርናው ምርታማነትና ለአካበቢ ስነ-ምህዳር መጠበቅ ወሳኝ ሚና እያበረከቱ ይገኛሉ ብለዋል። ይህም በመሆኑ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ስራው በክልሉ መንግስት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተመራ መሆኑንም አስረድተዋል። በተፈጥሮ ሀብት ልማት በአምስት ዓመታት ውስጥ ከተተከሉት የተለያዩ ዝርያ ያላቸው ችግኞች የጽድቀት ምጣኔያቸው የተሻለ መሆኑንም ተናግረዋል። ይህም የደን ሽፋኑን ቀደም ሲል ከነበረበት 17 በመቶ ወደ 27 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደጉን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማቱ የደረቁ ወንዞች፣ ጅረቶችና ሃይቆችን ከመመለስ ባለፈ በድርቅ ተጋላጭ የነበሩ የክልሉ አካባቢዎች በእንስሳት መኖ እንዲያከማቹ ማገዙን አስረድተዋል። የተፋሰስ ልማቱ ምርታማነትን ከመጨመር ባለፈ በንብ ማነብ፣ በመኖ አቅርቦትና በተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ የስራ ፈጠራ እድልን እየፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚህ አመትም ለ60 ቀናት የተፋሰስ ልማት ስራን ለማካሄድ መታቀዱንና ህዝቡ ለዚሁ ስራ በጉልበቱና በእውቀቱ የሚያበረክተው አስተዋጽኦም በገንዘብ ሲተመን ትልቅ መሆኑን አክለዋል። ዘንድሮ በ6 ሺህ 495 ተፋሰሶች ላይ በ3 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። ከተያዘው የጥር ወር አጋማሽ ጀምሮ እየተከናወነ ያለው የተፋሰስ ልማቱ ስራ ሳይንስዊ ይዘቱን ጠብቆ እንዲከናወን አመራሩና ባለሙያዎች እገዛ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
በክልሉ የተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ አድርገዋል - ኢንጂነር ምትኩ በድሩ(ዶ/ር)
Jan 30, 2025 87
ሺሾ-እንዴ፤ ጥር 22/2017(ኢዜአ)፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረጋቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የኢኮኖሚ አማካሪ ኢንጂነር ምትኩ በድሩ(ዶ/ር) ተናገሩ። በክልሉ የ"አፈር ሀብታችን ለብልጽግናችን" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው የዘንድሮው የበጋ ወቅት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ በካፋ ዞን ሺሾ እንዴ ወረዳ ተጀምሯል።   መርሃ ግብሩን ዛሬ በይፋ ያስጀመሩት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የኢኮኖሚ አማካሪ ኢንጂነር ምትኩ በድሩ(ዶ/ር) በክልሉ የተፈጥሮ ሀብትን መጠበቅና መንከባከብ የቆየ ልምድ አለ። ባለፉት ዓመታት ከ1 ሚሊዮን 745 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ በ1 ሺህ 64 ንዑስ ተፋሰሶች ላይ 185 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት ማልማት መቻሉን ገልፀዋል። በለሙ አካባቢዎችም ከ28ሺህ 700 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በመደበኛና በፕሮጀክቶች ወደ ስራ ገብተው እየተጠቀሙ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለ45 ቀናት በሚቆየው በዚህ የተፋሰስ ልማት ያረጁ ቡናዎችን የመጎንደል፣ የጉድጓድ ዝግጅት፣ የእርከንና ሌሎች ሥነ አካላዊ ሥራዎች እንደሚከናወኑም ተመላክቷል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የቀድሞው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የ11 ዓመት እስራት ተፈረደባቸው
Jan 30, 2025 78
አዲስ አበባ፤ ጥር 22/2017(ኢዜአ)፦ ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጋር ተያይዞ በሙስና በመደለል ከግብፅ መንግስት ጉቦ የተቀበሉት አሜሪካዊው የቀድሞው የኒው ጀርዚ ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የ11 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል። በኒው ዮርክ በ12 ዳኞች የተሰየመው ችሎት የፍርድ ውሳኔውን ትናንት ማስተላለፉን የአሜሪካው የቴሌቪዥን ጣቢያ ኤንቢሲ ዘግቧል። ችሎቱ ከዚህ ቀደም የ71 ዓመቱን የሕግ ባለሙያና ፖለቲከኛ በ16ቱም የሙስና ወንጀሎች ጥፋተኛ ብሏቸዋል። የአሜሪካ ፌደራል ዐቃቤ ሕጎች የቀድሞውን ሴናተር ጉቦ ተቀብለው የግብጽ ወኪል ሆኖ በመስራት፣ ፍትሕ እንዲዛባ በማድረግና የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወንጀል መክሰሳቸው ይታወቃል። ዐቃቤ ሕጉ ሜኔንዴዝ የአሜሪካ ሴኔት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሰብሳቢ በነበሩበት ወቅት የግብጽን ፍላጎት በማንጸባረቅ፣ ለዚህም ከግብጽ መንግስት ገንዘብ ማግኘታቸው በሰነድና በሰው ማስረጃ አረጋግጧል። የቀድሞው ሴናተር በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ጋር በተገናኘ በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ በኒው ጄርሲ በንግድ ስራ ላይ ከተሰማሩ 3 የግብጽ ሰዎች እጅ ወርቅ እና ጥሬ ገንዘብ ጉቦ ተቀብለዋል። ይህም ሴናተሩ ራሳቸውን ለግብጽ መንግሥት ወኪል አድርገው በመቆም ሰርተዋል የሚል ክስ ሲቀርብባቸው እንደነበረ ይታወቃል። በዚህም በዘረፋ፣ ጉቦ በመቀበል፣ ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም፣ በሴራ፣ ፍትህን በማደናቀፍና መሰል 16 ወንጀሎች ላይ ተሳትፎ ማድረጋቸው ተገልጿል። በ16 የሙስና ወንጀሎች ጥፋተኛ የተባሉት ሜኔንዴዝ የግብፅ መንግስት በሚሊዮን ዶላሮች የሚገመት የአሜሪካ መንግስት ወታደራዊ ድጋፍ እንዲያገኝ ረድተዋል የሚል ክስ እንደቀረባበቸውም እንዲሁ። ሜኔንዴዝ የውጪ መንግስታትን ፍላጎት ለማስፈጸም ከተቀበሏቸው ስጦታዎች መካከል 100 ሺህ ዶላር የሚያወጣ ወርቅና ቅንጡ መርሰዲስ መኪና የተጠቀሱ ሲሆን፣ በመኖሪያ ቤታቸውም 480 ሺህ ዶላር ጥሬ ገንዘብ በቤታቸው መገኘቱን የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ከዚህ ቀደም በስፋት ዘግበውታል። የቀድሞው ሴናተር ከግብጽ የንግድ ባለቤቶች ጋር የጥቅም ትስስር እንደነበራቸው ተጠቁሟል። በክሳቸው ላይ ከግብጽ በተጨማሪ ከሌሎች የውጭ መንግስታት ጉቦ መቀበላቸው በምርምራ እንደተረጋገጠም ተመላክቷል። እ.አ.አ በ2021 የ‘ኢትዮጵያ ስታብላይዜሽን ፒስ ኤንድ ዴሞክራሲ አክት’ ወይም ኤች አር 6600 ረቂቅ ሕግ ተጓዳኝ ወይም አጋዥ (ኮምፓኒየን ቢል) የሆነው የኢትዮጵያ ፒስ ኤንድ ዴሞክራሲ ፕሮሞሽን አክት ኦፍ 2022’ ወይም ‘ኤስ.3199’ የተዘጋጀው በ70 ዓመቱ ፖለቲከኛና የሕግ ባለሙያ ቦብ ሜኔንዴዝ ዋና አርቃቂነት ነው። በአሜሪካ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ረቂቅ ሕጎቹ በሕግ አውጪው አካል ድምጽ ተሰጥቶባቸው እንዳይጸድቁ ለማድረግ ሴናተሮችና የኮንግረስ አባላትን በማናገር፣ደብዳቤ በመጻፍ፣ፊርማ በማሰባሰብና በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ዘመቻ በማድረግ ጥረት አድርገዋል። ሕጉ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚጎዳና ሉዓላዊነቷን የሚጥስ እንደነበር በተደጋጋሚ ጊዜ ሲገለጽ ቆይቷል። እነዚህ ሕጎች እንዲፀድቁ ግብጽ ግፊት ስታደርግ እንደነበር ይታወቃል።
አሜሪካ ከዓለም ጤና ድርጅት አባልነት የመውጣቷን ውሳኔ ማጤን አለባት - የአፍሪካ ህብረት
Jan 22, 2025 179
አዲስ አበባ፤ ጥር 14/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት አሜሪካ ከዓለም ጤና ድርጅት አባልነት የመውጣት ውሳኔዋን እንድታጤነው ጠይቀዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ጉዳዩን አስመልክተው መግለጫ አውጥተዋል። በመግለጫቸውም አሜሪካ ከድርጅቱ አባልነት ለመውጣት መፈለጓ እንዳሳዘናቸው ሙሳ ፋኪ ገልጸዋል። ውሳኔውን መለስ ብሎ በማጤን በአባልነቷ ትቀጥላለች የሚል ተስፋ እንዳላቸውም አስታውቀዋል። አሜሪካ የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከል ማዕከል(አፍሪካ ሲዲሲ) መስረታ ላይ ቀደምት እና ጠንካራ ደጋፊ ነበረች ሲሉም በመግለጫቸው አስታውሰዋል፡፡ አሁን ላይ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዓለም አቀፉን የህብረተሰብ ጤና ደህንነት እንደ አንድ የጋራ ጥቅም የማረጋገጥ ተልዕኮውን ለመወጣት በዓለም ጤና ድርጅት ላይ ጥገኛ መሆኑን የገለፀው ህብረቱ፤ የድርጅቱ ቁልፍ መስራች አባል የሆነችው አሜሪካ ከተቋሙ የመውጣት ውሳኔዋን በድጋሚ እንድታጤነው ጠይቋል።
26ኛውን የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት የአፍሪካ አህጉራዊ ጉባኤን ኢትዮጵያ ታዘጋጃለች - ግብርና ሚኒስቴር  
Jan 15, 2025 190
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 26ኛውን የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት የአፍሪካ አህጉራዊ ጉባኤ ልታስተናግድ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት ጉባኤ በየዓመቱ በግንቦት ወር በፈረንሳይ ፓሪስ የሚካሄድ ሲሆን በየሁለት ዓመቱ ደግሞ በየአህጉራቱ እንደሚካሄድ ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በአፍሪካ ደረጃ 25ኛው ጉባኤ እአአ በ2023 ቦትስዋና ያስተናገደች ሲሆን 26ኛውን ጉባኤ ኢትዮጵያ እንድታዘጋጅ መመረጧንም አስታውቋል። ጉባኤው "የእንስሳት ጤና ለምግብና ስነ-ምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ለሕብረተሰብ ጤና" በሚል መሪ ሀሳብ ከጥር 27 እስከ 30/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል፡፡ ለጉባኤው መሳካት ከዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት ዋናው ጽህፈት ቤት፣ የአፍሪካ እና የምስራቅ አፍሪካ ተወካዮች ጋር የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶች ሲደረጉ መቆየታቸውም ተገልጿል። የግብርና ሚኒስቴርም ግብረ-ሃይል በማቋቋም ቅድመ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡ በጉባኤው ከየአፍካ ሀገራት የጤና ኃላፊዎችና ቋሚ ተወካዮች፣ ከዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት፣ በየአህጉሩ ያሉ የእንስሳት ጤና አመራሮች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍና የመንግሥት ተቋማት ተወካዮች እንደሚታደሙም ተጠቁሟል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) በጉባኤው በአፍሪካ የእንስሳት ጤና አገልግሎት፣ ድንበር ዘለል የእንስሳት በሽታዎችን መቆጣጠርና መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ብሎም ከበሽታ ነጻ የሆነ አህጉር ለመፍጠር የሚረዱ ውይይቶች ይደረጋሉ ብለዋል። በጉባኤው በእንስሳት ጤናና ልማት፣ በምግብና ስነ-ምግብ ዙሪያ የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እንደሚገኙና የተለያዩ ውሳኔዎች እንደሚተላለፉበት ገልጸዋል። በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እየተሰሩ ያሉ እንደ ዝርያ ማሻሻል፣ መኖ፣ የእንስሳት ጤና እና የሕብረተሰብ ጤና አጠባበቅ በስፋት ውይይት ይደረግባቸዋል፤ አቅጣጫዎች ይቀመጡበታል ሲሉም ተናግረዋል። የእንስሳት ጤና በንጥረ ነገር የበለጸገ ምግብ ለማምረት እንደሚረዳ፣ መቀንጨርን ከመከላከል አንጻር የእንስሳት ጤና ምን ያህል አስተዋጽኦ እንዳለውም የምናይበት መድረክ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራትና በአህጉር ደረጃ ካሉ ሀገራት ጋር ድንበር ዘለል የእንስሳት በሽታዎችን ለመቆጣጠር፣ የገበያ ተደራሽነትን ለማስፋት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋልም ብለዋል። ሀገራት ያላቸውን የእንስሳት በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ስትራቴጂና ተሞክሮ፣ ኢትዮጵያም በእንስሳት ጤና፣ መሰረተ ልማት እና ያሉ መልካም አጋጣሚዎችን ለዓለም የምታስተዋውቅበት፣ ልምድ የምንጋራበት መድረክ ነው ሲሉም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል። ከመቶ ዓመት የዘለለ የእንስሳት ጤና አገልግሎትና የምርምር ተቋማት፣ በእንስሳት ጤና ላይ ትኩረት አድርገው የሚሰሩ፣ ክትባትና መድሃኒት የሚያመርቱ፣ በእንስሳት ጤና የሰው ሃይል የሚያፈሩ ተቋማት መኖራቸው መልካም አጋጣሚዎች መሆናቸውንም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የሚካሄደው የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት የአፍሪካ ጉባኤ የእንስሳት ጤና እንዲጠበቅ ብሎም ዘርፉ እንዲነቃቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ማለታቸውም በመረጃው ተመላክቷል።
ሐተታዎች
በትናንት ታሪኳ ለአፍሪካ ነጻነት ውለታዋ፤ ዛሬ ደግሞ በብልፅግና ጉዞዋ ለኢትዮጵያ አድናቆትን የቸሩት የዚምባቡዌው አንጋፋ ፖለቲከኛ- ሲምበርሼ ሙቤንጌግዊ
Jan 31, 2025 112
የ79 ዓመቱ ዕድሜ ባለጸጋ ሲምበርሼ ሙቤንጌግዊ በትውልድ ሀገራቸው ዚምባብዌ ጉምቱ ፖለቲከኛና የዲፕሎማሲ ሰው ናቸው። በ1940ዎቹ አጋማሽ በቅኝ ገዥዎች አስተዳደር ዘመን የተወለዱት ሙቤንጌግዊ ግዛት ዘመን የተወለዱት የፖለቲካ ትግል የጀመሩት በሀገረ አውስትራሊያ የውጭ ሀገር ተማሪ እያሉ ነበር። ይሄውም በፈረንጆቹ 1960ዎቹ አንጋፋውን የዚምባብዌ የአፍሪካ ብሔራዊ አንድነት አርበኞች ግንባር ወይም የዛኑ ፒኤፍ ፓርቲ(Zimbabwe African National Union Patriotic Front- Zanu PF) የተማሪዎች ተወካይ እንዲሁም የኤዥያ ቀጣና ተወካይ ሆነው ነበር ንቅናቄውን የተቀላቀሉት። ሀገራቸው ከቅኝ ግዛት ነጻ እስከትወጣ ድረስ በተለያዩ ሀገራት የፖለቲካ ትግል ሲያደርጉ ቆይተው ድሕረ ነጻነት በዛኑ ፒኤፍ ማዕከላዊ ኮሚቴነትና በሌሎች የተለያዩ ከፍተኛ የፓርቲ አመራርነት ደረጃ አገልግለዋል። ዛሬም እያገለገሉ ነው። ሙቤንጌግዊ ከዘመነ ሮበርት ሙጋቤ ጀምሮ በዚምባብዌ የዲፕሎማሲ ታሪክ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት እና በተባበሩት መንግስታት ውስጥ ሀገራቸውን ወክለው ለረጂም ጊዜ በዲፕሎማትነት አገልግለዋል። በሚኒስትርነት ደረጃም በውጭ ጉዳይ፣ በማክሮ ኢኮኖሚክ ፕላኒንግና ኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን፣ በውሃ ሀብትና ልማት፣ በትራንስፖርት፣ በቤቶች ልማትና በሌሎች የሚኒስቴር ተቋማት ሚኒስትር ሆነው መንግስታዊ ሃላፊነቶች ተወጥተዋል። በዚምባብዌ ፓርላማ አባልነትና የቋሚ ኮሚቴዎች ሃላፊነትም እንዲሁ። ዛሬም በሀገሪቷ ገዥ ፓርቲ በሆነው በዛኑ ፒኤፍ ፓርቲ የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ዋና ጸሃፊ ሲሆኑ የሀገሪቷ ፕሬዝዳንት ከፍተኛ አማካሪ እንደሆኑም መረጃዎች ያሳያሉ። የኢትዮጵያዊያን የአርበኝነት መንፈስ ለፀረ ቅኝ ግዛትና አፓርታይድ ስርዓት ትግል እንዲቀጣጠል አድርጓል- የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል ከተለያዩ ሀገራት የመጡ እህት ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት መካሄድ መጀመሩ ይታወቃል። ከእንግዶቹ መካከልም የዚምባቡዌው ዛኑ ፒኤፍ ፓርቲ የውጭ ግንኙነት ዋና ጸሃፊ ሲምበርሼ ሙቤንጌግዊ ይገኙበታል። በአድዋ መታሰቢያ በተደረገው የጉባዔው መክፈቻ ላይ ተገኝተው የሀገሪቷን ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ እና የፓርቲያቸውን መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም ዛኑ ፒኤፍ ፓርቲ ኢትዮጵያ አፍሪካ ውስጥ ብቸኛዋ ቅኝ ገዢዎች ያልተንበረከከች ሀገር በመሆኗ ትልቅ አድናቆትና ዕውቅና ይቸራታል ብለዋል። የኢትዮጵያዊያን የአርበኝነት መንፈስ ለፀረ ቅኝ ግዛትና አፓርታይድ ስርዓት ትግል እንዲቀጣጠል ቁልፍ አበርክቶ እንደነበረው ጠቅሰዋል። አብዛኛው የአፍሪካ ነጻነት ትግሎች በኢትዮጵያዊያና በቆራጥ ኢትዮጵያዊያን ቁሳዊ፣ ሞራላዊና ዲፕሎማሲያዊ ድጋፎች የታጀቡ ነበሩ ብለዋል። የዚምባብዌ ነጻነት ሃይሎች ታሪክም ከዚህ የተለዩ አይደለም ያሉት ዋና ፀሐፊው፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጋዮች ከኢትዮጵያ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ስልጠናዎች እንዲሁም የጦር መሳሪያ ድጋፍ እንዳገኙ አውስተዋል። ዚምባብዌ ቅኝ ገዥዎችን ታግላ ድል ስትቀዳጅ የኢትዮጵያና የህዝቧን ውለታ እንደማትረሳ በመጠቆም። ፓርቲያቸው በብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ ሲጋበዝ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነጻነት የነበራትን ቁልፍ ሚና ዕውቅና በመስጠት የእንኳን ደስ አላችሁ ደስታውን ያበስራል ብለዋል። ጠቅላይ ሚነስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ብልፅግና በሀገር በቀል እሳቤ ሀገር ለመለወጥ የተነሳ ፓርቲ መሆኑን መጥቀሳቸውን አድንቀው፤ ሀገር የሚለወጠው በሀገሬው ሀሳብና በሀገሬው ሰው ሲመራ ነው የሚለውን የሀገራቸው ስነ ቃል አጣቅሰው የሀሳቡ ተጋሪ መሆናቸውን አስረድተዋል። ብልፅግና ፓርቲ በታሪካዊቷ ሀገር ኢትዮጵያ ሰላም፣ ልማትና ብልፅግና ለማምጣት በመታተር በአጭር ጊዜ ያሳካቸውን ድሎች አድንቀዋል። እስካዛሬ በርካታ ጉባዔዎችን ብታደምም እንደ ብልፅግና ፓርቲ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በማሳተፍ አካታችንቱን ያሳዬ ፓርቲ አላየሁም ሲሉ ለዲሞክራሲ ምህዳር መስፋት የተደረገውን ጥረት አወድሰዋል። የኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ በእርግጥም አስደናቂና የማይተማን ሲሉ አሞካሽተውታል። እንዴትስ ይህ ሁሉ ስኬት መጣ ሲሉ ተጠየቅ ሰንዝረዋል። በአዲስ አባባ ከተማ የተከናወኑ የልማት ስራዎች እኔን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የውጭ ዜጋ ያማለሉ ተጨባጭ የለውጥ ምስክሮች ናቸው ብለዋል። በርግጥም አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲና የሆነችውም በአጋጣሚ አይደለም፤ አዲስ አበባ ሁላችን የምንመካባት ውብ ከተማችን ናት ሲሉም በኩራት ተናግረዋል። በኢትዮጵያና በዚምባብዌ መንግስታት መካከል የሁለትዮሽ ዕውነተኛ ትብብር እንዲጎለበት እንዲሁም ከብልፅግና ፓርቲ ጋር የሚደረጉ የፓርቲ ለፓርቲ ግንኙነቶች ከምንጊዜውም በተሻለ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ሲምበርሼ ሙቤንጌግዊ አረጋግጠዋል።
የአንካራው ስምምነትና የኢትዮ- ሶማሊያ አጋርነት
Jan 27, 2025 99
በአፍሪካ ቀንድ በስትራቴጂክ አጋርነታቸው ስማቸው ጎልቶ የሚነሳው ኢትዮጵያና ሶማሊያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከወደብ ጋር ተያይዞ በመሃከላቸው ተፈጥሮ የነበረውን አለመግባባት ወደ ተርኪዬ አንካራ በመጓዝ በሰላም መቋጨት ችለዋል፡፡ ይህ አካሄድ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግር በራሳቸው መንገድ መፍታት እንደሚችሉ በድጋሚ ያሳዩበት አዲስ የግጭት መፍቻ መንገድ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በሶማሊያ የነበረው ውስጣዊ የሰላምና መረጋጋት ችግር ለአልቃይዳንና አልሸባብ አሸባሪ ቡድኖች መጠናከር ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሮ ቆይቷል። በቀጣናው የአሸባሪዎች እንቅስቃሴ ለአካባቢው አገራትም ስጋት በመሆኑ በትብብር መስራትን የሚጠይቅ ይሆናል። ለዚህም የኢትዮ - ሶማሊያ ግንኙነት መጠናከር የላቀ ትርጉም እንዳለው ይታመናል። ከመካከለኛው ምስራቅ አገራት በመቀጠል አፍሪካ በእርስ በርስ ግጭት የምትናጥ አህጉር ሆና ትጠቀሳለች። በአህጉሪቱ አሁን ላይ ከ35 በላይ የእርስ በርስ ግጭቶች መኖራቸው የሚጠቀስ ሲሆን በግጭቱ ውስጥም በርካታ የታጠቁ ሃይሎች ተሳታፊ መሆናቸው ይነገራል። ጉዳዩን አሳሳቢ የሚያደርገው በቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ፣ ሞዛምቢክ ፣ ናይጄሪያና ሶማሊያ የሚስተዋሉ ግጭቶችን የውጭ ሃይሎችም ሲያባብሱት ይስተዋላል። በመሆኑም የውስጥ ሰላምን ማስጠበቅና ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር ለዘላቂ መፍትሄ ወሳኝ አርምጃ መሆኑ ይታመናል። በኮሎምቢያ፣ ፊሊፔንስና አፍጋኒስታን ከተከሰቱት ግጭቶች አንጻር በአፍሪካ የሚታዩ ግጭቶችን በንግግር መፍታት ቀላል መሆኑን በተርኪዬ ሀልዱን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተባባሪ ፕሮፌሰር አህመት ዩሱፍ ይናገራሉ፡፡ ለዚህ ማሳያው ደግሞ ኢትዮጵያና ሶማሊያ ልዩነታቸውን በሰላም ለመፍታት በቅርቡ በአንካራ የደረሱበት ስምነት ነው ይላሉ ፡፡ ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት "ሁለቱ አገራት የደረሱበት ስምምነት በአፍሪካ ቀንድ ሊፈጠር ይችላል ተብሎ የተፈራውን ግጭት ያረገበ መሆኑን “ ኢማኑኤል ኦያንጎና ቱግሩል ኦጉዛን የተባሉ የአፍሪካ ጉዳይ ፀሃፊዎች ቲአርቲ በተባለ ድረ ገጽ ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ ጠቅሰዋል፡፡ ጉዳዩ በሰላም እልባት ማግኘቱ ያስደሰታቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረትና ኢጋድ ለሁለቱ አገራትና ለአደራዳሪዋ ለተርክዬ ምስጋናቸውን በማቅረብ እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የሶማሊያ ፈተና በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አልሸባብ የአፍሪካ ቀንድ አካባቢን የግጭት ማዕከል ለማድረግ በርካታ ሴራዎችን በመጠንሰስ ግጭት ጠማቂነቱን በግልጽ እያሳየ ይገኛል። ከዚህ ባለፈ ወደ ሶማሊያ እግራቸውን በማስገባት ላይ የሚገኙ አለም አቀፍ ተዋንያንና የተለያዩ አገራት ፍላጎታቸውን ለመጫን በሚያደርጉት ጥረት አገሪቱን ውጥረት ውስጥ ከተዋታል፡፡ በዚህ ረገድ በሶማሊያ የሰፈረው ሰላም አስከባሪ ኃይል ፈተና የተጋረጠበት ሲሆን ይህ እሽቅድድም ለአልሸባብ መጠናከር በር ይከፍታል የሚል ስጋት አሳድሯል። የዚያድ ባሬ መንግስት ከወደቀበት ጊዜ አንስቶ ሶማሊያ በእርስ በርስ ግጭት ስትናጥ ቆይታ በኋላም በአልሸባብ በእጅጉ እየተፈተነች ቢሆንም በተለይም የቁርጥ ቀን ጎረቤቷ ኢትዮጵያ በከፈለችው መስዋእትነት ህልውናዋ ተጠብቆ ቆይቷል። ኢትዮጵያ የሶማሊያን ሰላም ለማስጠበቅ ያሳየችው ቁርጠኝነትና በተግባርም የከፈለችው መስዋእትነት ቀላል የሚባልም አይደለም። የዲፕሎማሲ ስኬት ከአዲስ አበባ እስከ አንካራ ክፍተቱን መሙላት የተባበሩት መንግስታትና የአሜሪካ ሰላም አስከባሪ ሰራዊት አገሪቱን ለቀው ሲወጡ የተፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት ግንባር ቀደም ተሰላፊ የነበረችው ኢትዮጵያ መሆኗን ፀሃፊው ያስታውሳሉ ፡፡ እኤአ በ2005 የእስላማዊ ፍርድ ቤት ህብረት በአገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የጦር አበጋዞችን ድል በመንሳት እኤአ 2006 ላይ ስልጣኑን እንደተቆጣጠረ አዝሎት የመጣውን ስጋት ለማስወገድ ቀድማ የተገኘችው ኢትዮጵያ ነበረች፡፡ ኢትዮጵያ የአገሪቱን ሰላም በማስከበር ተልዕኮ ላይ ቆይታ እኤአ በ 2009 አገሪቱን ለቃ ስትወጣ የተከፈተውን ቀዳዳ በመጠቀም አልሸባብ የሶማሊያን ደቡባዊ ክፍል በመቆጣጠር የራሱን መንግስት ለማዋቀር በቅቷል፡፡ ቡድኑ እኤአ በ2012 ከአልቃኢዳ ጋር ያለውን አጋርነት በይፋ አደባባይ ካወጣ በኋላ የአለም ስጋት መሆኑ ታውቋል፡፡ አልሸባብ በኢትዮጵያ በደረሰበት ወታደራዊ ሽንፈት ለ18 አመታት በሶማሊያ ብሎም በጎረቤት አገር ኬኒያ ሲያደርስ የነበረውን ጥፋትና ስጋት በእጅጉ መቀነስ ተችሏል፡፡ ባለፉት 20 ዓመታት የሶማሊያን ሰላም በማረጋጋት፤ እንደ አልሸባብ ያሉ አሸባሪ ኃይሎችን በመዋጋትና ቀጣናዊ መረጋጋትን በመፍጠር የኢትዮጵያ ሠራዊትየላቀ ሚናውን መወጣቱን በርካቶች ያነሳሉ። የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላት የሆኑ ሃይሎች በዓባይ ጉዳይ በተለይም በህዳሴ ግድብ የጀመሩት የማሰናከል ዕርምጃ አልሳካ ሲል በሶማሊያ በኩል ኢትዮጵያ አፍንጫ ሥር ጦር ለማስፈር መፍጨርጨራቸው በኢትዮጵያ ላይ ቀጥተኛ የብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅም ሥጋት እንደሚደቅን ይታመናል፡፡ ይህ ደግሞ በአካባቢው ካለው የኃያላን አገሮች ጂኦፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነትና ዓለም አቀፍ የፀጥታ ችግር ጋር ተዳምሮ ቀጣናውን የከፋ ቀውስ ውስጥ ሊከት እንደሚችል እየተገለጸ ነው ፡፡ የሶማሊያ የሽግግር መንግሥት ኢትዮጵያ ወታደሮቿን እንድታስገባ ከጠየቀበት ጊዜ ጀምሮ ለአስራ ሰባት ዓመታት ያህል በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ስር በሚገኘው የሰላም አስከባሪ ኃይል ኢትዮጵያ ሰራዊቷን አሰማርታ መስዋዕትነት በመክፈል ላይ ትገኛለች። ኢትዮጵያ በአትሚስ ስር እንዲሁም ከሶማሊያ ጋር ባላት የሁለትዮሽ ስምምነት በብዙ ሺህ የሚቀጠር ሰራዊት በማሰማራት ለሶማሊያ ሉዓላዊነትና ለህዝቧቿ ደህንነት በዋጋ የማይታመን ከፍተኛ መስዋዕትነትን ከፍላለች። የአንካራ ስምምነት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼኽ ሞሐመድ፤ ታኅሣሥ 2 ቀን 2017 ዓ. ም. በቱርክ፣ አንካራ ስምምነት መፈረማቸው ይታወሳል። ስምምነቱ ኢትዮጵያ "በሶማሊያ ሉዓላዊ ሥልጣን ሥር አስተማማኝ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር መተላለፊያ" እንድታገኝ በቅርበት እንደሚሠሩ ተጠቅሷል። ከዚህ ባለፈ ውይይቱ ባለፈው አንድ ዓመት በሶማሊያ እና በኢትዮጵያ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ማስቻሉን አመልከተዋል። የኢትዮጵያ የባሕር የማግኘት ፍላጎት ጎረቤቶቻችንን ጭምር የሚጠቅም ሰላማዊ ጥረት ነው። ይህ ፍላጎት በትብብር መንፈስ እንጂ በጥርጣሬ ሊታይ አይገባውም" ሲሉ የአገራቸውን ፍላጎት ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጨምረውም "ገንቢ ውይይት" ኢትዮጵያ እና ሶማሊያን "በትብብር፣ በወዳጅነት እና በጠላትነት ሳይሆን በጋራ ለመሥራት ከሚኖር ፈቃደኝነት ጋር ወደ ቀጣዩ ዓመት ያሸጋግራል" ብለዋል። በኢትዮጵያና ሶማሊያ መካከል አንካራ ላይ የተደረሰው ስምምነት ከጋራ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ባሻገር አልሸባበን በጋራ ለመዋጋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ አልሸባብ አሁን ላይ የሶማሊያና ኢትዮጵያ ብሎም የቀጣናው ስጋት መሆኑን ሁሉም ያውቀዋል፡፡ በመሆኑም በአካባቢው ዘላቂ ሰላም ማስፈን የሚቻለው የጋራ ራዕይ በማንገብና በመከባበር ላይ የተመሰረተ ግንኙነትን በማጽናት ሲቻል መሆኑን በተርኪዬ ሀልዱን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተባባሪ ፕሮፌሰር አህመት ዩሱፍ ለቲአርቲ የሰጡት ማብራሪያ ያመልክታል።
ብቁ የሰው ኃይል ከማፍራት እስከ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ምርታማነት
Jan 20, 2025 132
የከተማ ግብርና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶት በግለሰብ መኖሪያ አካባቢና የተለያዩ ተቋማት ውስጥ እየተተገበረ ይገኛል። የትምህርት ተቋማትም በከተማ ግብርና ውጤታማ ስራ በመስራት ከሰራተኞቻቸው ፍጆታ አልፈው በተመጣጣኝ ዋጋ ለአካባቢው ማህበረሰብ እያቀረቡ ይገኛሉ። የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ካሉት የትምህርት ክፍሎች መካከል አንዱ የከተማ ግብርና ሲሆን በቅጥር ግቢው ውስጥ ለከተማ ግብርና ቦታ በመወሰን የተቀናጀ ግብርና በውጤታማነት እየሰራ ነው። በዚህም የወተት ላም እርባታ፣የከብት ማድለብ ስራ፣ የጓሮ አትክልት፣ የአሳ እርባታና የዶሮ እርባታ ይገኙበታል። በኮሌጁ የከተማ ግብርና ትምህርት ክፍል ኃላፊ አሰልጣኝ ታሪኩ በቀለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኮሌጁ ከሚሰጣቸው ስልጠናዎች ባሻገር በተግባር በሌማት ትሩፋት ውጤታማ ስራዎችም እየሰራ ይገኛል። ኮሌጁ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ዘመናዊ የወተት ልማት ማዕከል ገንብቶ ስራ መጀመሩን ጠቁመው ኮሌጁ ለሚሰጣቸው ስልጠናዎች የተግባር ልምምድ የሚካሄድበት ብሎም የወተት ምርት ለግቢው ማህበረሰብ በዝቅተኛ ዋጋ ተደራሽ እየተደረገበት ነው ብለዋል፡፡ ኮሌጁ እያከናወነ ያለው የከተማ ግብርና ስራዎችን ሰልጣኞች በተጨባጭ የልምምድ ተግባር የሚያከናወኑበት ከመሆን ባለፈ የተቋሙን ሰራተኛ መደጎም አላማ ያደረገ መሆኑንም ጠቁመው፥ ለአብነትም ወተት በሊትር እስከ 30 ብር በመሸጥ ላይ መሆናቸውን ይናገራል። በዚህም ከወተት በወር 110 ሺህ ብር ገቢ በማግኘት ላይ መሆናቸውን ጠቁመው፥ በዓመት ከ1 ሚሊዮን 320 ሺህ ብር በላይ ገቢ እንደሚያስገኝም ጠቁመዋል፡፡ በተቋሙ በሚገኘው የጓሮ አትክልት እርሻም ተማሪዎች ተመርቀው የራሳቸውን ስራ እስኪጀምሩ ድረስ ስራውን እንዲከታተሉና ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ተቋሙ የዶሮ፣ የእንቁላል፣ የእርድ ሰንጋዎች፣ የወተት እና አጠቃላይ የጓሮ አትክልቶች ለሽያጭ በማቅረብ ገቢ እያገኘበት እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለጻም፥ የከተማ ግብርና ስራዎቹ ከተግባር ስልጠና ባሻገር የሚገኘውን ምርት ለአካባቢው ማህበረሰብና ለተቋሙ ሰራተኞች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ የኮሌጁ የአሳ እርባታ ማዕከልም የአሳ ጫጩቶችን መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት በማከፋፈል ተጨማሪ ገቢ በማግኘት ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ የከተማ ግብርና የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አኳያ ትልቅ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት በዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ውጤታማነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚችሉም መክረዋል፡፡  
የዲፕሎማሲ ስኬት ከአዲስ አበባ እስከ አንካራ
Dec 31, 2024 337
ኢትዮጵያና ሶማሊያ በአንካራ ያደረጉት ስምምነት በአፍሪካ ቀንድ የሰላም እና የልማት ትብብርን ለማጠናከር እንደማሳያ ይወሰዳል፡፡ ምንም እንኳን ከራሳቸው የግል ስውርና የገሀድ ፍላጎት መነሻነት የሁለቱን ሀገራት ስምምነት ሊያጣጥሉ የሚሞክሩ አንዳንድ የውጭ ሀይሎች ቢኖሩም የአንካራው ስምምነት ከሁለቱ ሀገራት ፍላጎትና ጥቅም የተሻገረ ቀጣናዊ ትሩፋት ያለው ነው። የአንካራው ስምምነት ይዘቶች፣ ለሁለቱ ሀገራት እና ለቀጣናው የሚኖረው በረከት እና የስምምነቱን ተፈጻሚነት የማይፈልጉ ሃይሎች አካሄድ ምን እንደሚመስል እንዲሁም ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም፣ ልማትና ትብብር ላይ እስካሁን ያደረገችውን አበርክቶ ለመቃኘት እንሞክር። ኢትዮጵያ በአፍሪቃ ቀንድ ቀጣና የአፍሪካ ቀንድ ከ170 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርበት ቀጣና ነው። ቀንዱ ከቀይ ባሕርና ሕንድ ውቅያኖስ የሚያገናኘውን የዓለማችን ስትራቴጂካዊ ስፍራ በመያዙ ለዓለም የስበት ማዕከል ሆኗል። ቀጣናው ፖለቲካዊና ምጣኔ ሀብታዊ ጠቀሜታው ጉልህ ነው። በቀይ ባህር በየዓመቱ በሺህዎች የሚቆጠሩ መርከቦች እንደሚተላለፉበት መረጃዎች ያመላክታሉ። የዓለምን 12 በመቶ የወደብ ገበያ ይሸፍናል። በዚህም ምክንያት ብሄራዊ ጥቅማቸውን ለማሳካት የሚሹ የሩቅም የቅርብም ጠላትና ወዳጅ ሀገራት አካባቢውን ለመቃኘት የሚያባክኑት ሽርፍራፊ ሰከንድ የለም። ሁሌም በአካባቢው የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን አይናቸውን ሳይነቅሉም ክትትል የሚያደርጉበት ቀጣና ነው። ቀጣናው የሃያላን ቀጥተኛና ኢ-ቀጥተኛ ዕጆች የሚበዙበት በመሆኑም ቀጣናውን ኢ-ተገማችና ተለዋዋጭ መልክ እንዲይዝ አድርጎታል። ይህ ደገሞ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ልማትና ትብብር ዋጋ እየከፈለች ላለችው ኢትዮጵያ ፈተና መደቀኑ ዕሙን ነው። ኢትዮጵያም ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር፣ ሰላምና ትብብር በየዘመኑ ከፍተኛ ዋጋ ስትከፍል ቆይታለች። ለአብነትም በመሰረተ ልማት ረገድ በድንበር ተሻጋሪ የባቡር፣ የመንገድ እና የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማት በማስተሳሰር በኩል የኢትዮጵያ ሚና ከማንም የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካም ሆነ በዓለም ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ በመሳተፍ ለሰላም እና ለነጻነት መከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ለአፍሪካ ብሎም ለዓለም ሰላምና ደህንነት መከበር የላቀ ውለታ ውላለች። በተለይም በምስራቅ አፍሪካ ለጎረቤት ሀገራት ሠላም መጠበቅ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍላለች። ሶማሊያ፣ ሱዳንና ደቡብ ሱዳን ለዚህ አብነት የሚሆኑ ሀገራት ናቸው። ለሀገራቱ ሰላም መከበር በከፈለችው ዋጋም ሀገራቱ ከግጭት ቀውስ እንዲወጡ፣ መንግሥታቱ በሁለት እግራቸው እንዲቆሙ አድርጋለች። ሶማሊያ አጣብቂኝ ውስጥ በገባችበት ወቅት ሁሉ ኢትዮጵያ በሚቀብላት ጥያቄ መሰረት አልሻባብን በመዋጋት ህዝቡን ከዕልቂት ሀገሪቱንመ ከመበታተን ታድጋለች። ኢትዮጵያ ለሀገራት ሰላምና ደህንነት ለተጫወተችው ሚናም ዓለም አቀፍ ዕውቅና ተችሯታል። ዛሬም ለቀጣናው ሠላም፣ የጋራ ልማትና ትብብር ሌት ተቀን እየሠራች ትገኛለች። በቅርቡ ከሶማሊያ ጋር የተደረሰው የአንካራው ስምምነት ኢትዮጵያ ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ያላትን የጸና አቋምና ቁርጠኝነት ያሳየችበት የዲፕሎማሲ ድል ነዉ። የአንካራው ስምምነት-የዲፕሎማሲ ስኬት ማሳያ በያዘነው ታኅሣሥ ወር መባቻ ላይ በቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን አሸማጋይነት የተደረገው የአንካራ ስምምነት በኢትዮጵያና ሶማሊያ መካከል ተፈጥሮ የነበረውን አለመግባባት የቀረፈ ስምምነት ነው። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ሰላምና ትብብርን የሚያጎለብት፣ የሀገራቱን ሕዝቦች ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክር፣ ለቀጣናው ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና የሚበጅ ሲሉ በርካቶች ታሪካዊ ስምምነት እንደሆነ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት፣ የአውሮፓ ሕብረትና ኢጋድ አድንቀውታል። እንግሊዝ፣ ጀርመንና አሜሪካን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስምምነቱ ለቀጣናው ያለውን ፋይዳ በማውሳት አሞካሽተውታል። በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ ሀገሪቱን ወደቀይ ባህር የመለሰ ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ድል ተሰኝቷል። በቀጣናው ሰላም የከፈለችውን ዋጋም ዕውቅና ያሰጠ ነው። የአንካራ ስምምነት ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታገኝ ለምታደርገው ጥረት በር ከፋች ሆኗል። በዚህም የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት መሻት ዓለም አቀፍ ዕውቅና እንዲያገኝ አስችሏል። በዚህም የኢትዮጵያ የወደብ ጥያቄ ህጋዊ ሞራላዊ እና ፖለቲካዊ መሰረት ያለው ነው። ይህም ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ የዘርፉ ምሁራንም ስምምነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር ለወዳጅ ሀገራት ጭምር ተስፋ የፈነጠቀ ክስተት ነው፡፡ ስምምነቱ ለአደራዳሪዋ ቱርኪዬ ጭምር የዲፕሎማሲ ተቀባይነቷን ያሳደገ ነው። ቱርኪዬ በአፍሪካ ቀንድ ለምታደርገው ተሳትፎ መሸጋገሪያ ድልድይ እንደሚሆናት ተንታኞች ይናገራሉ። በጥቅሉ ስምምነቱ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው በመጥቀስ ኢትዮጵያ ሚዛን የሚደፋ ድል እንድትቀዳጅ አስችሏታል ይላሉ። የፀረ-አንካራ ስምምነት ሃይሎች ስምምነቱ ቀጣናውን ለማተራመስ ስውር ዓላማ ሰንቀዉ ለሚንቀሳቀሱ አካላት ራስ ምታት ሆኗል። ዓለም በአንድ ድምጽ ያደነቀውን፣ የቀጣናውን ሠላም በማስጠበቅ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የዓለም ሀገራት እና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች እየመሰከሩለት ያለውን ይህን ስምምነት ከአላስፈላጊ ጣልቃ ገብነት ለመጠበቅ የሁሉንም ርብርብ ይፈልጋል፡፡ ስምምነቱ የቀጣናውን ሰላም እና መረጋጋት የማይሹ አካላት እኩይ አላማ ያከሸፈ ነዉ፡፡ ሆኖም እነዚህ አካላት በሚያገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስምምነቱ ግቡን እንዳይመታ መጣራቸው የማይቀር ነው፡፡ የሁለቱ ሀገራት ስምምነት እንዳይሰምርም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሶማሊያ ላይ በሚያሳድሩት አሉታዊ ጫና ዋና እና ተጎጂ ሶማሊያ እና የሶማሊያ ህዝብ መሆናቸው የእነዚሁ አካላት የቀደሙ ጣልቃ ገብነቶች ያስከተሉት ጉዳት ጥሩ ማሳያዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሃይሎች ለሶማሊያውያን አንድነት እና ሰላም ከፍተኛ ዋጋ የከፈለውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በማጥላላት በየሚዲያዎቻቸው የሚያናፍሱት መሰረተ ቢስ መረጃ በሁለቱ ሀገራት ስምምነት እኩይ አላማቸው ላይሳካ በአጭር መቀጨቱን የሚያሳይ ነው:: የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ ከሶማሊያ ጋር ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደሚያጤኑት መግለፃቸው በአሸዋ መሰረት ላይ የገነቡት ሴራ መፍረሱን የሚያመላክት ሆኖም ታይቷል፡፡ እነዚህ አካላት ሶማሊያ በከፋ የውስጥ ችግር ውስጥ በነበረችበት ወቅት አይተው እንዳላየ ሲያልፉ ቢቆዩም የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ግን ለሶማሊያ መጠናከር እና የውስጥ ሰላም መስፈን የሚያደርጉት ድጋፍ ጊዜ እንደማይሽረው እና ጥቅም እንደማይለውጠው በተግባር የታየ ሀቅ ነው፡፡ የአንካራው ስምምነትም በደምና በመስዋዕትነት የተሳሰረው የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ወንድማማችነት ቢቀጥንም የማይበጠስ መሆኑን አመላካች ነው ላይበጠስም ተቋጥሯል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 572
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 795
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 1017
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 2368
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 749
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 2158
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
   ያ ሆዴ የአዲስ ብርሃን ተስፋ
Sep 21, 2024 3989
በማሙሽ ጋረደው ከሆሳዕና የኢዜአ ቅርንጫፍ ከብት የሚጠብቁ ህፃናት አዲስ ዓመት እየመጣ ስለመሆኑ ማብሰሪያ ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ የዋሽንት /የገምባቡያ/ ድምፅ ማሰማት ይጀምራሉ። በመስከረም ከጉምና ጭጋግ ፀለምት ጨለማ የሚወጣበትና ምድሩ በአበባ ሀምራዊ ቀለም የሚታጀብበት ወቅት በመሆኑ በሀዲያ ብሄር ዘንድ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ወቅት ነው። ያ ሆዴ የሀዲያዎች አዲስ የዘመን መለወጫ በዓል መባቻ ነው። ያ ሆዴ ማለት በሀዲያዎች ዘንድ “ብርሃን ሆነ፣ መስቀል መጣ፣ ገበያው ደራ፣ በይፋ ተበሰረ ብሎም እንኳን ደስ አላችሁ” የሚል ስያሜ እንዳለውም ይነገራል። “ያ ሆዴ " በሀዲያ ካሉ እሴቶችና ወጎች እንዲሁም ክንዋኔዎች መካከል አንዱ ሲሆን፤ አንድነት፣ መቻቻል፣ ለውጥን ለማሳለጥ፣ አብሮነትና ሰላም ለማጠናከርም ከፍተኛ ሚና እንዳለው ይወሳል። የሀዲያ አገር ሽማግሌ አቶ መንገሻ ሂቤቦ እንዳጫወቱን ከሆነ ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ ከብት የሚጠብቁ ህፃናት አዲስ ዓመት መምጣቱን የዋሽንት /የገምባቡያ/ ድምፅ በማሰማት አዋጅ ማብሰር ይጀምራሉ። ይህም የበዓሉ መቅረብን ለማሳሰብና ለማስታወቅ የሚደረግ ነው። በዓሉ ብርሃን፣ብሩህ ተስፋ፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ረድኤት በረከት የሚሞላበት ተምሳሌታዊ ወር ተደርጎ ይታመናል። ያ ሆዴ በሀዲያ ዘንድ ልዩ ስፍራ የሚሰጠው በዓል ነው። በዓሉ ከመድረሱ በፊት ሁሉም የቤተሰብ አባላት በዓሉን ለማድመቅ የየራሳቸው ድርሻ አላቸው። ለምሳሌ አባት ለእርድ የሚሆን ከብት በማቅረብ፣ እናት ደግሞ ሌሎች የቤት ስራዎች በማከናወንና ልጆችም ልዩ ልዩ የስራ ድርሻቸውን በመወጣት በዓሉን ያከብራሉ። “አባቶች አብሮነታቸውን ከሚያጠናክሩባቸው ማህበራዊ እሴቶች መካከል አንዱ ቱታ /ሼማታ/ ነው” ይላሉ የሀዲያ አገር ሽማግሌ አቶ መንገሻ፤ ይህም ከአራት አስከ ስምንት አባላትን ይዞ የሚደራጅ የስጋ ማህበር ነው። የማህበሩ አባላት ግንኙነት ያላቸው የሚተሳሰቡ የኢኮኖሚ አቅማቸውም ተቀራራቢነት ያለው ሲሆን፤ በዓሉ ከመድረሱ በፊት በጋራ ገንዘብ ማስቀመጥ ይጀምራሉ። ለስጋ መብያ የሚሆን ቆጮ ብሎም ለአተካና የሚሆን ቡላ በማዘጋጀት ከጥቅምት እሰከ ጥር ባሉት ወራት ውስጥ እንሰት በመፋቅ እናቶች በቡድን ተሰባስበው ዝግጅታቸውን ማከናወን ይጀምራሉ። በተጨማሪም ዊጆ |የቅቤ እቁብ| በመግባት ቅቤ በማጠራቀም ለበዓሉ አስፈላጊ የሆኑ ቅመማ ቅመሞችን በማዘጋጀት ኃላፊነታቸውን ይወጣሉ። የዳጣ፣ የአዋዜ ዝርያዎችንና ለበዓሉ ማድመቂያ የሚሆኑ ባህላዊ የሆኑ መጠጦችን ጭምር ያዘጋጃሉ። ልጃገረዶች በዓሉ እንዲደምቅ ቤት መደልደል፣ የተለያዩ ቀለማትን በመጠቀም የግርግዳ ቅርጻ ቅርጾችን በመስራት እንዲሁም ግቢ በማጽዳት የማሳመር ስራቸውን ያከናውናሉ። ወጣት ወንዶች ለማገዶ የሚያገለግል በአባቶች ተለይቶ የተሰጣቸውን እንጨት ፈልጠው እንዲደርቅ ያደርጋሉ። ጦምቦራ ለደመራ የሚሆን ችቦ በማዘጋጀት ግዴታቸውን ይወጣሉ። የሀዲያ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ባለሙያ ወይዘሮ አመለወርቅ ሃንዳሞ እንደሚሉት፤ በዓሉን ለማክበር በአገር ውስጥ የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆች ወደ ቤተሰቦቻቸው በመመለስ አብሮነት ለማክበር ከእሩቅም ከቅርብም ይሰበሰባሉ። ይህም በዓሉ ለአብሮነትና ለሰላም ያለውን ፋይዳ የላቀ ያደርገዋል። ዓመቱን ሙሉ ለበዓሉ የሚደረጉ ዝግጅቶችና የስራ ክፍፍሎች ልዩ ትርጉም ያላቸው ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ “ወጣቶች የትዳር አጋራቸውን የሚመርጡበት በመሆኑ በዓሉን ልዩ ድባብ ይሰጠዋል” ይላሉ ወዘሮ አመለወርቅ። የበዓሉ ዋዜማ /ፉሊት ሂሞ/ ወጣቶች ያዘጋጁትን ጦምቦራ /የደመራ ችቦ/ የአካባቢውን ነዋሪዎች በሚያዋስን ቦታ ላይ ይሰራሉ። እናቶች ከቡላ፣ ቅቤና ወተት የሚያዘጋጁት ጣፋጭ የሆነ እና ጣት የሚያስቆረጥመውን አተካና በማዘጋጀት የበዓሉን ዋዜማ/ፉሊት ሂሞን/ ያደምቁታል። የበዓሉ አመሻሽ ዋዜማ ላይ ወጣቶች “ያ ሆዴ ያ ሆዴ “በማለት ይጨፍራሉ። ይህም ለበዓሉ “የእንኳን አደረሳችሁ” መልእክት አለው። በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የአገር በቀል እውቀቶች ምርምር ዳይሬክተር አቶ እያሱ ጥላሁን “ይህ በዓል የሚሰጠው የስራ ክፍፍል፣ የሰላምና አብሮነት ዕሴቶች ለጠንካራ ዕድገት፣ ነገን በተስፋ ለመመልከት ወሳኝ ነው” በማለት ይገልጹታል። በወቅቱ ወጣቶች በአካባቢው እየዞሩ በመጫወት ከአባቶች ምርቃት ይቀበላሉ። የአካባቢው ነዋሪዎች ደመራው በተዘጋጀበት ቦታ ማምሻውን ይሰባሰቡና አባቶች ደመራውን የሚያቀጣጥሉበትን ችቦ በመያዝ ልጆችን በማስከተል ዓመቱ የብርሃን፣ የሰላም፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እንዲሆን ፈጣሪያቸውን በመማጸን ደመራውን ይለኩሳሉ። ደመራው ተቀጣጥሎ እንዳለቀ በእድሜ ከፍ ወዳሉ አባወራ ቤት እንደሚሰባሰቡ ነው አቶ እያሱ የተናገሩት። የእርድ ስርዓቱ በሚከናወንበት ቤት ደጃፍ አባላቱ ቤተሰቦቻቸውን በመያዝ በአንድነት በመሰባሰብ የጋቢማ ስርዓት ይከናወናል። ይህም እድሜ ጠገብ ሽማግሌዎች ቅቤ እና ወተት በሚታረደው በሬ ላይ እያፈሰሱ” ለምለም ሳር "በመያዝ በሬውን እያሻሹ አዲሱ ዓመት ለህዝብ እና መንግስት የሰላም ዓመት የሚመኙበት መንገድ ነው። ልጆች ለወግ ለማዕረግ የሚበቁበት፣ መካኖች የሚወልዱበት፣ የተዘራው ለፍሬ የሚበቃበት ዓመት እንዲህን ፈጣሪያቸውን ይማፀናሉ። በሦስተኛው ቀን የቱታው አባላትና የአካባቢ ሰዎች ተጠርተው በአባቶች ምርቃት ተደርጎ በአንድነት ሆነው ምክክር በማድረግ ለቀጣይ ዓመት የሚሆን እቅድ በማዘጋጀት ተጨዋውተው ይለያያሉ። “በየቤቱ የሄደው ቅርጫ በፍጹም ለብቻ አይበላም” ያሉት አቶ እያሱ፤ በየአከባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችን አፈላልጎ ማብላትና ማጠጣት በማከናወን በዓሉን በጋራ ያሳልፋሉ። ይህም በዓሉ አንዱ ለአንዱ ያለውን ወዳጅነትና አብሮነትን በማጠናከር ትስስርን የማጉላት አቅሙ ከፍተኛ ነው። በሌላ በኩል ተጣልቶ የከረሙ ነዋሪዎች ከተገኙ በሰከነ መንፈስ በመነጋገር እርቀ ሰላም በማውረድ በንጹህ ህሊና፣ በአዲስ ምዕራፍ፣ በአዲስ ተስፋና በአዲስ መንፈስ አዲሱን ዓመት ይጀምራሉ። ይህም “ባህሉ በዜጎች መካከል የሰላምና አብሮነት ምሰሶ መሆኑን ያመለክታል” ያሉት አቶ እያሱ፤ በንጹህ ልቦና በብርሃንና በተስፋ መጪውን ዘመን ለማሳለፍ እንዲቻል ጉልህ ሚና እንዳለው አጽንኦት ይሰጡታል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 44269
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 37877
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 26387
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 23731
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 22015
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 20410
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 20000
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 19607
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 44269
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 37877
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 26387
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 23731
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ኢትዮጵያ እና የሕብረቱ ወሳኝ አካል የሆነው ምክር ቤት
Jan 17, 2025 335
  የአፍሪካ ሕብረት ቁልፍ ተቋም ነው- የሕብረቱ የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት። የፊታችን የካቲት ወር መጀመሪያ ሳምንት ላይ በሚደረገው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባዔ ከሚቀረቡ ዝርዝር አጀንዳዎች አንዱ የዚህ ምክር ቤት አባላት ምርጫ እንደሚሆን ይጠበቃል። ኢትዮጵም በቅርቡ ለምክር ቤቱ አባል ለመሆን ፍላጎቷን ይፋ አድርጋለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ አባል ለመሆን ያላትን መሻት በአዲስ አበባ ለሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች አብስረዋል። ለመሆኑ የሕብረቱ የሰላምና የደህንነት ምክር ቤት ስራው ተልዕኮና ሚና ምንድነው? አባላቱም እንደ ሀገር ምን ፋይዳ ይሰጣቸው ይሆን የሚለውን እንናስቃኝዎ!   የምክር ቤቱ ለመመስረቻ ጥንስስ የተጠነሰሰውና የማቋቋሚያ ሕግ ማዕቀፍ የጸደቀው በአውሮፓዊያኑ 2002 በደርባን(ደቡብ አፍሪካ)በተካሄደው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ ስብስባ ነበር። በአውሮፓዊያኑ ታኅሣሥ 2003 ወደ ስራ ገባ። ባለፈው ዓመት (ግንቦት 2016 ዓ.ም) ምክር ቤቱ 20ኛ ዓመት የምስረታ ቀኑን በአዲስ አበባ አክብሯል። ምክር ቤቱ በአህጉሪቷ ግጭቶች እንዳይከሰቱ አስቀድሞ መከላከል፣ የግጭት አስተዳደርና አፈታት ላይ ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። በአህጉሪቷ ለሚከሰቱ ግጭቶች ጊዜውን የጠበቀ እና በቂ ምላሽና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል። ለአፍሪካ የሰላም እና ደህንነት ማዕቀፍ (African Peace and Security Architecture) ቁልፍ ምሰሶ ነው። የምክር ቤቱ አወቃቀር፣ ተልዕኮና ሚና ከአወቃቅር አኳያ ምክር ቤቱ ዕኩል ድምጽ ያላቸው 15 አባል አገራት ይኖሩታል። አባላቱም በሕብረቱ የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ይመረጣሉ። በመሪዎች ጉባዔ አባልነታቸው ይጸድቃል። ከአባላቱ መካከል አምስቱ ለሶስት ዓመታተ፤ ቀሪዎቹ ለሁለት ዓመታት የሚቆይ ስልጣን አላቸው። ምክር ቋሚ አባል አገር የለም። የአባልነት ጊዜ የጨረሱ ሀገራት ግን ድጋሚ የመመረጥ መብት አላቸው። አባላት የሚመረጡት ግን በቀጣናዊ ውክልና እና በተራ ቅደም ተከተል መርህ ነው። ይኼውም ማዕከላዊ፣ ምሥራቃዊ፣ ደቡባዊ እና ሰሜናዊ ቀጣናዎች ሶስት አባል ሀገራት ሲሆኑ የምዕራብ ቀጣና ግን አራት አባል አገራት ይኖራቸዋል። በምክር ቤት ሕገ ደንብ መሰረት ለምክር ቤቱ አባል ለመሆን ቅድመ ሁኔታዎች አሉ። ይሄውም የአፍሪካ ሰላምና ደህንነትን በማስተዋወቅና በማረጋገጥ ያለው አስተዋጽኦ፣ በቀጣናዊና በአህጉር አቀፍ ደረጃ በሰላም ማስከበር እና በሰላም መፍጠር ውስጥ ያለው ሚና፣ ቀጣናዊና አህጉር አቀፍ የግጭት መፍቻ ኢኒሺቲቮች ለመሳተፍ ያለው ፍላጎት እና ኃላፊነት ለመውሰድ ያለው ቁርጠኝነት፣ ለአፍሪካ ህብረት የሰላም ፈንድ የሚያደርገው አስተዋጽኦ፣ ለሕገ መንግስት አስተዳደር፣ የሕግ የበላይነት እና የሰብዓዊ መብቶች ያለው ከበሬታ እንዲሁም ለአፍሪካ ሕብረት የፋይናንስ መዋጮ ግዴታዎች ያለው ተገዢነት እና ቁርጠኝነት አንድን አገር አባል ሆኖ እንዲመረጥ የሚያስችሉት መስፈርቶች ናቸው። ምክር ቤት ከሕብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ጋር በመጣመር ከስር የተመላከቱ ስልጣንና ተግባራቱ ተሰጥቶታል። . ዘር ማጥፋትና በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሊያመራ የሚችል የግጭት አዝማሚያን መተንበይ፣ አስቀድሞ በመከላከልና የግጭት መንስዔዎችን ለይቶ ፖሊሲ መቀየስ። የጦር ወንጀሎች፣ ዘር ማጥፋት እና የሰብዓዊነት ወንጀሎች ሲፈጸሙ ለመሪዎች ጉባዔ ሕብረቱን ወክሎ ጣልቃ መግባት የሚችልበትን ምክረ ሀሳብ ያቀርባል። . ለግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ በማስቻል ሰላም መገንባት ላይ ይሰራል።የአፍሪካ ሕብረት አጠቃላይ የጋራ የመከላከያ ፖሊሲ ይተገብራል። . ለሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ፈቃድና ስምሪት ይሰጣል፤ የሰላም አስከባሪ ኃይል የስራ ኃላፊነት ጨምሮ ተልዕኮውን የተመለከቱ መመሪያዎችን ያወጣል። . በአፍሪካ ሕብረት አባል አገራት ኢ-ሕገመንግስታዊ የመንግስት ለውጥ ሲኖር ማዕቀብ ይጥላል። . የፀረ-ሽብርተኝነትን ዓላም አቀፍ ስምምነቶች የአባል ሀገራት ትግበራን ይከታተላል። በመልካም አስተዳደር፣ በሕግ የበላይነት፣ የሰብዓዊ መብቶች እና መሰረታዊ ነጻነቶች እና ሰብዓዊ መብቶች ላይ ጥበቃ ያደርጋል። ቀጣናዊና አህጉራዊ የተቀናጀ የሰላምና ደህንነት አሰራርን መፈጸሙንም እንዲሁ። በጦር መሳሪያ ቁጥጥርና ትጥቅ የማስፈታት የሕግ ማዕቀፎችን ትግበራ ይደግፋል። . የአፍሪካ ሕብረት አባል አገራትን ነጻነት እና ሉዓላዊነትን ስጋት ላይ የሚጥሉ የኃይል እርምጃዎችን በመመርመር እርምጃ ይወስዳል። . በሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ወቅት ለሰብዓዊ ድጋፍ ያስተባብራል። አፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የሰላምና ደህንነት የስራ ክፍል ውስጥ የሚገኘው የምክር ቤቱ ሴክሬተሪያት ለምክር ቤቱ የኦፕሬሽን ስራዎች የቀጥታ ድጋፍ ያደርጋል። ምክር ቤቱ በአህጉሪቷ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓት፣ “Panel of the Wise” በተሰኘው የአፍሪካ ሕብረት የማማከር አደረጃጀት፣ በአፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል እና የሕብረቱ የሰላም ፈንድ ድጋፍ ይደረግለታል። በምክር ቤቱ በስሩ ያሉት ወታደራዊ አባላት እና የባለሙያዎች ቡድን ኮሚቴዎች፣ የአፍሪካ የሰላምና ደህንነት ማዕቀፍ (APSA)፣ የአፍሪካ የሴቶች ግጭት መከላከል እና የሰላም ድርድር ኔትወርክ (FemWise–Africa) እንዲሁም የሰላምና ደህንነት ማስከበር ተልኮዎች ሌሎች ደጋፊ አካላት ናቸው። ምክር ቤቱ ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ተቋማት እና ከሌሎች ቀጣናዊ አደረጃጀቶች ጋር ግጭትን አስቀድሞ መከላከል፣ አስተዳደር እና መፍትሄ ላይ በጋራ ይሰራል። ከተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት እና ሌሎች መሰል ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እንዲሁም ፓን-አፍሪካ ፓርላማ እና የአፍሪካ የሰብዓዊና የህዝብ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ ከሌሎች የአፍሪካ ህብረት አደረጃጀቶች ጋር በሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይም በትብብር እየሰራ ይገኛል። የአፍሪካ የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት ኃላፊነቶች፣ አደረጃጀቶች እና የቅንጅት አሰራር ማዕቀፎች በአህጉሪቷ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ያለውን ቁልፍ የውሳኔ ሰጪነት አቅም የሚያሳይ ነው።   ኢትዮጵያ እና ምክር ቤቱ ኢትዮጵያ ለመወዳደር የፈለገቸው ለሶስት ዓመት (በአውሮፓዊያኑከ2025 እስከ 2027) ድረስ ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮች ለአፍሪካ የዋለችውን ታሪካዊ ሚና ከግንዛቤ በማስገባት በውሳኔ ሂደቱ ድጋፋቸውን እንዲሰጡ ጠይቀዋል። በርግጥ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ያላት ቁልፍ ሚና ተገቢነቱ አያጠራጥርም። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሰላምና መረጋጋት ለረጅም ዘመናት በቁርጠኝነት ሰርታለች። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ ሄኖክ ጌታቸው (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት የአፍሪካ ሕብረት የሰላምና ደህንነት ምክር ቤት አባል ሆና ማገልገሏን ያስታውሳሉ። ምክር ቤቱ የአሁኑን ስያሜውን ከማግኘቱ በፊት በቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ማዕቀፍ ከእ.አ.አ 1993 እስከ 2000 ባለው ጊዜ አባል ሆና ማገልገሏን ገልጸዋል። በአፍሪካ ሕብረት ደግሞ በአውሮፓዊያኑ ከ2004 እስከ 2010 እንዲሁም ከ2014 እስከ 2016 አገልግላለች። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ አባል ሆና ብትመረጥ ብሔራዊና ቀጣናዊ ፍላጎቶቿንና ጥቅሞቿን ከማስጠበቅ እና አንጻር ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እንደምታገኝ ሄኖክ(ዶ/ር) ይናገራሉ። የምክር ቤቱ አጀንዳዎች ከብሔራዊ ጥቅሞቿ ጋር አጣጥሞ ለመሄድና ፍላጎቶቿን የሚጻረሩ ጉዳዮች ለመከላከል ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርላትም በማንሳት። የአፍሪካ ዋንኛ የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ አብዛኛውን ትኩረቱን አፍሪካ ቀንድ ከማድረጉ አንጻር ኢትዮጵያ በአካባቢው ባሉ ጉዳዮች ላይ ያላት ሚና እንዲጎለብት አስተዋጽኦ ያደርጋል ነው ያሉት ከፍተኛ ተመራማሪው። ቀጣናው ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታና ዓለም አቀፍ ትኩረትን የሚስብ መሆኑ ያሉ ችግሮች መፍትሄ እንዲያገኙ የበኩሏን ድርሻ መወጣት እንደምትችልም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ አባልነት የሕብረቱ የመመስረቻ ቻርተርና የህግ ማዕቀፎች እንዲጠበቁ፣ አህጉራዊ አጀንዳዎችን ለማራመድ፣ ሰላምና ጸጥታን ለማስፈንና በቀጣናው ከምትጫወተው ሚና አንጻር በርካታ ጠቃሜታዎችን እንደምታገኝ ተናግረዋል። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ አባል ለመሆን የተሻለ የተወዳዳሪነት ብልጫ እንዳላት ያነሳሉ። ለምን ቢባል አንድም ኢትዮጵያ በሩዋንዳ፣ በሱዳን፣ በደቡብ ሱዳን፣ በላይበሪያ፣ በኮንጎ፣ በሶማሊያ እና በሌሎች የአፍሪካ አገራት በሰላም ማስከበር ተሳትፎ በማድረግ ያላት ልምድ ነው። አንድም የአፍሪካ ሕብረት ዋና መቀመጫ መሆኗና ከዚህ ቀደም በምክር ቤቱ የነበራት ግልጋሎት እንደ የተወዳዳሪነት ብልጫ እንድታገኝ ያስችላታል። አባልነቷን ለማረጋገጥ ግን ከሀገራት ጋር የሁለትዮሽ ውይይቶችና ሌሎች የተቀናጀ የዲፕሎማሲ ስራ ማከናወን ይጠበቃል ይላሉ። ምከር ቤቱ በሕብረቱ የሰላም እና የደህንነት ምክር ቤት የአፍሪካ የሰላምና ደህንት ጉዳዮች ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪ አካል በመሆኑ አባል ብትሆን ካላት ታሪካዊ አበርክቶ አኳያ ይበልጥ ለአህጉራዊ ሰላምና ደህንነት ገንቢ ሚና እንደምትጫወት ዕሙን ነው።
ወንዞቿን ከብክለት ወደ ትሩፋት ለመለወጥ የተነሳችው አዲስ አበባ
Jan 13, 2025 282
  አዲስ አበባ ከተቆረቆራች አንድ ከግማሽ ምዕተ ዓመት ልትደፍን ጥቂት ዓመታት ይቀራታል። ከተማዋ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ዑደት አስኳል ሆና ሁሉን አስተናግዳለች።   ዕድል ቀንቷት ከኢትዮጵያዊያን አልፋ የአፍሪካዊያን መዲና ሆናለች። ዘመን ችሯት የዓለም ዲፕሎማሲ ማዕከል አድርጓታል። ከአፍሪካ ወደ ዓለም፤ ከዓለም ወደ አፍሪካ መግቢያና መውጫ በር ናት። የሀገሪቷ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ዕድገት የስበት ማዕከል ናት። በፍጥነት ያደገችና ነዋሪቿን ያበዛች፤ ምጣኔ ሀብትን ያጎለመሰች ከተማ ናት። ዳሩ የከተሜነት መዋቅራዊ ፕላኗ አኳያ ውስንነቶች እንደሚስተዋልባት በባለሙያዎች ዘንድ ይነሳል። ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ዘመን ተሻጋሪ፣ ለኑሮ ምቹና ስሟን የሚመጥን የክትመት ዕቅድ ይዛ ባለመጓዟ ውበትም፤ ኑረትም፣ ምቾትም አጉድላለች። በጽዳትና ውበቷ ረገድ በእንግዶቿም ዘንድም ለትቸት ተጋልጣ ታውቃለች። ከአዲስ አበባ ድክመቶች አንዱ የብዙ ወንዞች ባለቤት ሆኗ አንዱንም እሴት ጨምራ ወደ ሀብትትነት አለመቀየሯ ነው። ፈሳሽ ወንዟን አልምታ በውበት አለመፍሰሷ። በመዲናዋ ከ76 ያላነሱ ዋና እና ገባር ወንዞች ይገኛሉ። ዳሩ በየዘመኑ የከተማ ልማት ዕቅዶች የወንዝ ዳርቻን ታሳቢ ባለማድረጋቸው ወንዞቿ ለገጽታዋ ውበት ሳይሆን ሳንካ ሆነዋታል። የከተሜነት ወጓ ከወንዞቿ ልማት ጋር አልተመራም። የሰዎች አሰፋፈር ከዓለም አቀፋዊ የከተሜነት ልክን አልጠበቀም። ይህ ደግሞ ወንዞች ለነዋሪዎቿ ጠንቅ እንጂ ትሩፋት እንዳይሆኑ አድርጓል። በርካታ ሀገራት ከተሞች ጥቂት ወንዞቻቸውን ለጌጥም፤ ለበረከትም አውለዋል። ባለበዙ ወንዞች ባለቤቷ አዲስ አበባ ግን "ጽድቁ ከርቶ..." እንዲሉ ከወንዞቿ ጥቅሟ ቀርቶ፤ ጠንቋ በዝቶ ቆይታለች። ወንዞቹን ለምተው ለዘርፈ ብዙ አገልግሎት ከመዋል ይልቅ ለብክለት ተጋልጠው ለሕዝብ ጤና ጠንቅ ነበሩ። በክረምት ወራትም ጎርፍ እየተሞሉ ነዋሪዎችን ለአደጋ አጋልጠዋል። እነሆ አሁን የዘመናት ክፍተቷን ለመቅረፍ ተነስታለች። ከተማ አቀፍ የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ተጀምረዋል። የመዲናዋን ወንዞች ከሕዝብ ጤና ጠንቅነት ወደ ጥቅም የመለወጥ ተግባር እየተከናወነ ይገኛል። በአዲስ አበባ ከሚፈሱ ወንዞች መካከል እስካሁን አንድ ወንዝ ለቱሪስት መስህብነት፣ ለመዝናኛነትና ለሌላ አገልግሎት ለማዋል የተሰራ የተፋሰስ ልማት እየተከናወነ ነው። የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የበርካታ ሀገራት ከተሞች የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ወንዞችን አልምተው ለቱሪስት መነሃሪያ እንዲሆኑ በማስቻል ለቱሪዝም ዘርፍ እመርታ ወሳኝ ድርሻ እንዲይዙ ማድረጋቸውን ይጠቅሳሉ። አዲስ አበባ ግን በርካታ ወንዞችን ታቅፋ ይህን መልካም ዕድል አልምታ ሳትጠቅም በመቆየቷ ቁጭት የሚፈጥር ጉዳይ እንደሆነ ያነሳሉ። እናም እየተከናወነ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት የህብረተሰቡን አኗኗር ብቻ ሳይሆን ለተፋሰስ ልማትም ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ወንዞች ከጠንቅነት ወደ ህዝብ ጥቅምነት የመለወጥ ስራዎች እንደቀጠሉ ከንቲባዋ አብስረዋል። በዚህም አዲስ አበባ ካሏት 76 ወንዞች መካከል አንድ ሶስተኛው ትልልቅ ወንዞቿ ለቱሪስት መዝናኛ አገልግሎት መዋል የሚችሉ ናቸው ብለዋል። ከነዚህም መካከል እስካሁን ሁለት ወንዞችን በወንዝ ዳርቻ ልማት በማስገባት ወደ ዘርፈ ብዙ ጥቅም የመለወጥ ጉዞ መጀመሩን ተናግረዋል። በትናንትናው ዕለት የከተማዋ አመራሮች እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማቶችን ጎብኝተው ነበር። ከተጎበኙ የከተማ ልማት ስራዎች መካከል የቀበና ቁጥር-1 እና 2 እንዲሁም ከእንጦጦ-ፍሬንድ ሽፕ- ፒኮክ የወንዝ ዳርቻ ልማት ይገኝበታል። ከንቲባዋ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የወንዝ ዳርቻ ልማት ከብክለት ነጻ አካባቢን በመፍጠር፣ ከተማዋን ጽዱና አረንጓዴ በማድረግና በሽታን በመከላከል ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል። የእንጦጦ-ፍሬንድ ሽፕ- ፒኮክ የወንዝ ዳርቻ ልማት የተለያዩ ፓርኮችን በማስተሳሰር በፕላን የተገነባ ከተማን እውን ማድረግ የሚያስችል እንደሆነ በማብራራት። በቀበና ቁጥር 2 እንዲሁም ከእንጦጦ- ፍሬንድ ሽፕ- ፒኮክ የወንዝ ዳርቻ አፍንጮ በር አካባቢ የመጓተት ችግሮችን በመቅረፍ ስራው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። 70 ደረጃ እና 40 ደረጃ ታሪካዊ ቅርስነታቸውን ጠብቀው እየታደሱ እንደሚገኙ ገልጸው፤ ከዕይታ ተደብቆ የቆየውን የራስ መኮንን ሀውልት ከቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ዕድሳት ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ፒያሳ አካባቢ እየተሰራ የሚገኘው የወንዝ ዳርቻ ልማት አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የሩጫ፣ የሳይክል፣ የመዋኛና ሌሎች ቦታዎችን ነው። ልማቶቹ አለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችንና ሁነቶችን ለማስተናገድ የሚያስችሉ እንደሆኑ ከንቲባዋ በጉብኝቱ ወቅት አብራርተዋል። የህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሾች፣ ፓርኪንግ፣ የታክሲ ተርሚናል፣ ሱቆችንና ሌሎች ልማቶችን አካቶ እየተሰራም ነው። ፕላኑን የጠበቀ ዘመናዊ ከተማን እውን የሚያደርግ ከንቲባዋ ጠቁመዋል። የወንዝ ዳርቻን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አቀፍ የልማት ስራዎች ዘመናዊ ከተማን ያሟሉ በመሆኑ ለአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ይጨምራሉ።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም