ኢትዮጵያ የወደፊት የሚያልሙ አሳቢ ወጣት ዜጎቿ ተስፋ አላት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2016(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የወደፊት የሚያልሙ አሳቢ ወጣት ዜጎቿ ተስፋ አላት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ በይፋ የጀመርነው የ''አምስት ሚሊዮን ኮደርስ'' መርሃግብር ታላቅ እድል ነው ብለዋል።


 

ወጣቶች በመርሃግብሩ በመመዝገብ ክሂሎት እንዲያገኙና አለምአቀፍ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዲያገኙ ሁሉም እንዲያበረታታ ጥሪ አቀርበዋል።

ለታላቁ የአቅም ግንባታ ፕሮጀክት ትብብር የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግሥትን አመስግነዋል።


 

አምስት ሚሊዮኖቹ ኮደርስ ሀገር በቀል መፍትሔዎችን የሚሰጡ ብቻ ሳይሆኑ ለአህጉራችን የተስፋ ብርሃን የሚፈነጥቁም ናቸው ሲሉም ገልጸዋል።

 

 

 

 

 

 

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም