አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በሱዳን የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛን ተቀብለው አነጋገሩ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 26/2016(ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በሱዳን የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ቶም ፔሪሎ ጋር ተወያዩ።

ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ በሆኑ ጉዳዮች እና በተለይም በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ምክክር አድርገዋል።


 

በሱዳን ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማድረግ ላይ ስለሚገኙት ጥረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታዬ ለልዩ መልዕክተኛው ገልፀዋል።

በወቅቱ በሱዳን ሰላም እና ፀጥታን በዘላቂነት ለማስፈን በጋራ ለመስራት ሁለቱ ወገኖች መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም