የፒፕልስ ራሊ ፎር ፕሮግረስ ፓርቲ ዋና ፀሐፊ እና የጅቡቲ ፋይናንስ ሚኒስትር ኢልያስ ሙሳ ዳዋሌህ ምን አሉ

 

👉ኢትዮጵያ ሁሌም የቀጣናው ምሰሶ፤ የሰላም ዘብ እና የቀጣናዊ ትስስር ትዕምርት ናት። በቀጣናው እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ወሳኝ ሚና ያላት ሀገር ናት።

👉 አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የአፍሪካ መዲናም ናት። አዲስ አበባ እንደ ስሟ ዛሬ አዲስ ሆናለች።

👉 ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠንካራ አመራር ሰጪነት በፈጣን ለውጥ ላይ ናት። በአስገራሚ ሁኔታ ወደ ዘመናዊ ከተማነት እየተቀየረች ነው።

👉 ጅቡቲ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ናት።

👉 ጅቡቲ ጠንካራ፣ ሰላማዊ እና በኢኮኖሚ የተሳሰረ ቀጣና ለመፍጠር በትብብር ከኢትዮጵያ ጋር ትሰራለች። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት በቀጣይ ዕጣ ፈንታ እና የጋራ ህልሞች ለማሳካት መስራት ይገባቸዋል።

👉በአድዋ ድል መታሰቢያ በመገኘቴ ትልቅ ኩራት ይሰማኛል። አድዋ የአይበገሬነት፣ አንድነት እና የአሸናፊነት መንፈስ ተምሳሌት የሆነ ቦታ ነው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም