የሱዳን ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ (ኤስፒኤልኤም) ዋና ፀሐፊ ፒተር ላም ቦዝ ምን አሉ - ኢዜአ አማርኛ
የሱዳን ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ (ኤስፒኤልኤም) ዋና ፀሐፊ ፒተር ላም ቦዝ ምን አሉ
![](/documents/42135/0/475832804_1048972840607663_478361111539606524_n.jpg/98cb81e6-ff69-cf35-fb71-9ecbe10df707?version=1.0&t=1738409285967&download=true)
የኢትዮጵያ እና የደቡብ ሱዳን የሁለትዮሽ ትብብር እና የግንኙነት አድማስ እያደገ መጥቷል። የናይል ትብብር ማዕቀፍ የሁለቱ ሀገራት ትስስር ዋንኛ ማሳያ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ የኢትዮጵያ መሪዎች ለደቡብ ሱዳን ላደረጉት ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ምስጋናዬን ላቀርብ እወዳለሁ። እ.አ.አ በ2025 ብቻ 632 ደቡብ ሱዳናውያን በኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል አግኝተዋል።
ብልጽግና ፓርቲ ቃል የገባቸውን ተግባራት የፈጸመበት መንገድ እጅግ የሚደነቅ እና ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው።
አዲስ አበባ በመሰረተ ልማት ግንባታ ከፍተኛ ለውጥ እያሳየች ነው። በከፍተኛ ሁኔታ ተቀይራለች። ፒያሳ ደማቅ ውበትን ተጎናጽፋለች።
ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ በመሰረተ ልማት፣ በወደብ አገልግሎት፣ ትራንስፖርት፣ ኢነርጂ እና በኃይል ማመነጫ ግድብ ግንባታ ያላትን ትብብር ማጠናከር ትሻለች።