የተርኪዬ ኤኬ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዛፈር ሲራካያ ምን አሉ - ኢዜአ አማርኛ
የተርኪዬ ኤኬ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዛፈር ሲራካያ ምን አሉ
ኢትዮጵያ ከዓለማችን ጥንታዊ ስልጣኔዎች አንዷ ናት። ኢትዮጵያ በአፍሪካ የታሪክ ገጾች ውስጥ ጉልህ ታሪክ የጻፈች እንዲሁም በባህል፣ በታሪክ፣ በብዝሃነት፣ በእምነት፣ በቋንቋና ቅርስ የበለጸገችና በፈተናዎች ሳትበገር ዘመናትን የተሻገረች ሀገር ናት።
ተርኪዬና ኢትዮጵያ የነጻነትና ሉዓላዊነት የአይበገሬነት መንፈስ የሚጋሩ ሀገራት ናቸው። ኢትዮጵያ እና ተርኪዬ በታሪክ ጥብቅ ቁርኝነት አላቸው። ተርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር አጠናክራ ትቀጥላለች።
ኢትዮጵያ እና ተርኪዬ በዘመናት መካከል የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸው እና ትብብራቸው እያደገ መምጣቱንና በርካታ ስኬቶች እያስመዘገበ ይገኛል።
ተርኪዬ ለቀጣናው ሰላምና ልማት መረጋገጥ አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ያነሷቸው ሃሳቦች ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ቀጣናውና የአፍሪካን ብልፅግናን ዕውን ማድረግ የሚያስችሉ ናቸው።