ከናይጄሪያው ኤፒሲ ፓርቲ ምክትል ሊቀ-መንበር አልሀጅ አሊቡካር ዳሎሪ መልዕክቶች - ኢዜአ አማርኛ
ከናይጄሪያው ኤፒሲ ፓርቲ ምክትል ሊቀ-መንበር አልሀጅ አሊቡካር ዳሎሪ መልዕክቶች
ኢትዮጵያና ናይጄሪያ በመከባበር እና በጋራ እሴት ላይ የፀና ለበርካታ ዓመታት የዘለቀ ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው።
ሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲ፣ ንግድ እና ባህል ጨምሮ በተለያዩ መስኮች አጋርነት አላቸው።
ሁለቱ ሀገራት የተለያዩ ፈተናዎች ቢያጋጥማቸውም ችግሮችን ለመፍታት ያለው ብቸኛ አማርጭ ትብብር እና አጋርነት ነው።
ኤፒሲ እና ብልጽግና ፓርቲ የጋራ ግብ ያላቸው ፓርቲዎች ናቸው።
ሁለቱም ፓርቲዎች ልማትን ለማረጋገጥ፣ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን እና የበለጸገ ሀገር ለመፍጠር እየሰሩ መሆናቸው ያላቸውን የአላማ አንድነት ያሳያል።
የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ ልማትና አንድነትን ለማምጣት ያለንን ቁርጠኝነት በጋራ የምናወድስበት ነው።
የናይጄሪያው ኤፒሲ ፓርቲ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ ይቀጥላል።